“ምርጫው በሠላም በመጠናቀቁ ተደስተናል” – የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሠላማዊ መንገድ በመካሄዱ መደሰታቸውን የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።
አቶ ዮሴፍ ስለሺ፣ አቶ ታየ ገብረማርያም፣ ወ/ሮ ምህረት ይስሃቅ እና አቶ ምስክር ዘለቀ
በሰጡት አስተያየት፤ ምርጫው በሠላማዊ መንገድ መከናወኑን ተናግረዋል።
በምርጫ ቦርድ የሰዓት ጭማሪ ምክንያት እስከ እኩለ ለሊት ድረስ ሥርዓት ባለው መንገድ መምረጣቸውን አስታውቀዋል።
የምርጫ ቦርድ ሰራተኞች፣ የፀጥታ አካላት፣ የምርጫ ታዛቢዎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ተወጥተዋል ነው ያሉት።
የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ለአቅመ-ደካሞችና ለአካል ጉዳተኞች ቅድሚያ ተሰጥቶ መከናወኑን ጠቁመዋል።
በቦንጋ ከተማ አስተዳደር በአብዛኞቹ ምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ ቆጠራ ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ተመራጮችና መራጩ ህዝብ የምርጫው ጊዜያዊ ውጤት ይፋ እስኪሆን በትዕግስት መጠባበቅና ሲገለፅም በፀጋ መቀበል እንዳለባቸው አስተያየት ሰጥተዋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ ክፍሌ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሌሞ 01 ምርጫ ክልል በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት እየተለጠፈ ይገኛል
ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት ይፋ መደረግ ጀምሯል
በሀዲያ ዞን ሶሮ 02 ምርጫ ክልል ጃጁራ ከተማ አስተዳደር የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት ይፋ መሆን ጀምሯል