“ምርጫው በሠላም በመጠናቀቁ ተደስተናል” – የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሠላማዊ መንገድ በመካሄዱ መደሰታቸውን የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።
አቶ ዮሴፍ ስለሺ፣ አቶ ታየ ገብረማርያም፣ ወ/ሮ ምህረት ይስሃቅ እና አቶ ምስክር ዘለቀ
በሰጡት አስተያየት፤ ምርጫው በሠላማዊ መንገድ መከናወኑን ተናግረዋል።
በምርጫ ቦርድ የሰዓት ጭማሪ ምክንያት እስከ እኩለ ለሊት ድረስ ሥርዓት ባለው መንገድ መምረጣቸውን አስታውቀዋል።
የምርጫ ቦርድ ሰራተኞች፣ የፀጥታ አካላት፣ የምርጫ ታዛቢዎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ተወጥተዋል ነው ያሉት።
የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ለአቅመ-ደካሞችና ለአካል ጉዳተኞች ቅድሚያ ተሰጥቶ መከናወኑን ጠቁመዋል።
በቦንጋ ከተማ አስተዳደር በአብዛኞቹ ምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ ቆጠራ ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ተመራጮችና መራጩ ህዝብ የምርጫው ጊዜያዊ ውጤት ይፋ እስኪሆን በትዕግስት መጠባበቅና ሲገለፅም በፀጋ መቀበል እንዳለባቸው አስተያየት ሰጥተዋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ ክፍሌ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ በ2018 በጀት አመት ከ336 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ሀብት ከምዝበራና ከብክነት ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ከ45.7 ቢሊየን ብር በላይ በጀት አፀደቀ
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት