የተርጫን ለኑሮ ምቹና ተመራጭ እንድትሆን ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን በማከናወናቸው የተሻለ ለውጥ እየታየ ነው – የከተማዋ አስተዳደር ከንቲባ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 11/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የተርጫ ከተማን ለኑሮ ምቹና ተመራጭ እንድትሆን ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን በማከናወናቸው የተሻለ ለውጥ እየታየ መምጣቱን የከተማዋ አስተዳደር ከንቲባ ገለፁ፡፡
ካለፉት ዓመታት ይልቅ አሁን በመሠረተ ልማት ዝርጋታ መሻሻሎች መኖራቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡
በመንግሥትና በኅብረተሰብ ተሳትፎ እየተገነቡ የሚገኙት የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎችን የከተማው ነዋሪዎች በመጠበቅ እና በመንከባከብ የድርሻቸውን መወጣት አለብን በማለት ነዋሪዎቿ ተናግረዋል፡፡
የተርጫ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ባቲሣ ወንድሙ እንደሚሉት በከተማዋ የነዋሪዎቿን የልማት ፍላጎት ለመመለስና የመኖሪያ ቤት ባለቤትነት ጥያቄን ለመመለስ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል፡፡
በተለይም ከከተማዋ ዕድገት ጋር ተያይዞ የሚታየውን ፈጣን ለውጥ አጠናክሮ ለማስኬድ የነዋሪዎቿ ብርቱ ጥረት እንደሚፈልግም አቶ ባቲሣ አሳስበዋል፡፡
የታርጫ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዳዊት በበኩላቸው በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ለመንገድ ከፈታና ጠጠር ማልበሻ፣ ለጎርፍ መውረጃና ፍሳሽ ማሰወገጃ ቦይ ግንባታ፣ ለመንገድ ዳር መብራት ዝርጋታ፣ የአረጋውያን መኖሪያ ግንባታ እና መሠል የልማት ተግባራት ከ34 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የልማት ተግባራቱ እየተከናወኑ መገኘታቸውን አስረድተዋል፡፡
በፌዴራልና በክልል መንግሥታት ወጪ ከ2 መቶ 15 ሚሊዮን ብር በላይ እየተገነባ የሚገኘው የንጹሕ መጠጥ ውሃ ግንባታና ዝርጋታ በተያዘለት የጊዜ ገደብን እንዲጠናቀቅ የሚያስችሉ የድጋፍ ሥራዎችም እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡
መሣይ መሰለ ከዋካ ቅርንጫፍ

More Stories
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት
መደበኛ ባልሆነ መልኩ የሎተሪ ዕድል ሙከራን “ዕቁብ” በሚል ሽፋን በህገ-ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት አሳሰበ
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ