የሀዲያ ዞን ትምህርት ቤቶችን መሠረተ-ልማት ለማሻሻል የተዘጋጀ የህዝብ ንቅናቄ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 11/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሀዲያ ዞን ትምህርት ቤቶችን መሠረተ-ልማት ለማሻሻል የተዘጋጀ የህዝብ ንቅናቄ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በዞኑ የኢንስፔክሽን አገልግሎት ካገኙ ትምህርት ቤቶች መካከል 87 ከመቶ እንዲሁም ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል 60 ነጥብ 6 በአጠቃላይ 83 ነጥብ 6 ከመቶ ትምህርት ቤቶች በትምህርት መሠረተ-ልማት ግብዓት ከደረጃ በታች መሆናቸው የተገለፀ ሲሆን በጉዳዩ ላይ ትኩረት ያደረገ የህዝብ ንቅናቄ መድረክ ነው እያተካሄደ የሚገኘው።
መድረኩም “ትምህርት ለሁሉም” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ሲሆን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም መጫን ጨምሮ ሁሉም የትምህርት ባለድርሻ አካላት ተሳትፏል።
ዘጋቢ፡ አለቃል ደስታ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የብልጽግና ፓርቲ 3ኛው ዙር ስልጠና አካል የሆነው የመስክ ጉብኝት በዲላ ከተማ ተካሂዷል
የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 መከበሩ የእርስ በርስ አንድነትን የሚያጠናክር መሆኑን በ20ኛዉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ላይ የተሳተፉ ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ ልዑካን አባላት ተናገሩ
በጎፋ ዞን ስልጠና እየወሰዱ ያሉ የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች በደንባ ጎፋ ወረዳ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል