የሀዲያ ዞን ትምህርት ቤቶችን መሠረተ-ልማት ለማሻሻል የተዘጋጀ የህዝብ ንቅናቄ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 11/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሀዲያ ዞን ትምህርት ቤቶችን መሠረተ-ልማት ለማሻሻል የተዘጋጀ የህዝብ ንቅናቄ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በዞኑ የኢንስፔክሽን አገልግሎት ካገኙ ትምህርት ቤቶች መካከል 87 ከመቶ እንዲሁም ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል 60 ነጥብ 6 በአጠቃላይ 83 ነጥብ 6 ከመቶ ትምህርት ቤቶች በትምህርት መሠረተ-ልማት ግብዓት ከደረጃ በታች መሆናቸው የተገለፀ ሲሆን በጉዳዩ ላይ ትኩረት ያደረገ የህዝብ ንቅናቄ መድረክ ነው እያተካሄደ የሚገኘው።
መድረኩም “ትምህርት ለሁሉም” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ሲሆን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም መጫን ጨምሮ ሁሉም የትምህርት ባለድርሻ አካላት ተሳትፏል።
ዘጋቢ፡ አለቃል ደስታ – ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
የመልካም አስተዳደር ችግሮች ተቀርፈው ህብረተሰቡ ተገቢ አገልግሎት እንዲያገኝ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
በጉራጊኛ ቋንቋ የሚጻፉ መጽሐፍት ለቋንቋው እድገት፣ መልማት፣ መበልጸግና ወደ ትውልዱ ለማድረስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው – ረዳት ፕሮፌሰር ካሚል ኑረዲን
የ”ባለ ካዳቤ” በዓል የዕርቅ፣ የፍቅር፣ የአንድነትና የብርሃን ተምሳሌት መሆኑ ተገለጸ