የሀዲያ ዞን ትምህርት ቤቶችን መሠረተ-ልማት ለማሻሻል የተዘጋጀ የህዝብ ንቅናቄ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 11/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሀዲያ ዞን ትምህርት ቤቶችን መሠረተ-ልማት ለማሻሻል የተዘጋጀ የህዝብ ንቅናቄ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በዞኑ የኢንስፔክሽን አገልግሎት ካገኙ ትምህርት ቤቶች መካከል 87 ከመቶ እንዲሁም ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል 60 ነጥብ 6 በአጠቃላይ 83 ነጥብ 6 ከመቶ ትምህርት ቤቶች በትምህርት መሠረተ-ልማት ግብዓት ከደረጃ በታች መሆናቸው የተገለፀ ሲሆን በጉዳዩ ላይ ትኩረት ያደረገ የህዝብ ንቅናቄ መድረክ ነው እያተካሄደ የሚገኘው።
መድረኩም “ትምህርት ለሁሉም” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ሲሆን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም መጫን ጨምሮ ሁሉም የትምህርት ባለድርሻ አካላት ተሳትፏል።
ዘጋቢ፡ አለቃል ደስታ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ ባለፉ 6 ወራት ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ
ዘመናዊ የግብርና ግብአት እና ቴክኖሎጂን በተገቢው በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ የቀቤና ልዩ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለፀ