የሀዲያ ዞን ትምህርት ቤቶችን መሠረተ-ልማት ለማሻሻል የተዘጋጀ የህዝብ ንቅናቄ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 11/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሀዲያ ዞን ትምህርት ቤቶችን መሠረተ-ልማት ለማሻሻል የተዘጋጀ የህዝብ ንቅናቄ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በዞኑ የኢንስፔክሽን አገልግሎት ካገኙ ትምህርት ቤቶች መካከል 87 ከመቶ እንዲሁም ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል 60 ነጥብ 6 በአጠቃላይ 83 ነጥብ 6 ከመቶ ትምህርት ቤቶች በትምህርት መሠረተ-ልማት ግብዓት ከደረጃ በታች መሆናቸው የተገለፀ ሲሆን በጉዳዩ ላይ ትኩረት ያደረገ የህዝብ ንቅናቄ መድረክ ነው እያተካሄደ የሚገኘው።
መድረኩም “ትምህርት ለሁሉም” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ሲሆን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም መጫን ጨምሮ ሁሉም የትምህርት ባለድርሻ አካላት ተሳትፏል።
ዘጋቢ፡ አለቃል ደስታ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ