ነገ ለሚተከለው አንድ ቀን አረንዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ማለዳ በነቂስ ወጥተው ለመትከል መዘጋጀታቸውን የደቡብ ኦሞ ዞን ነዋሪዎች ገለፁ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 09/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ነገ ለሚተከለው አንድ ቀን አረንዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ማለዳ በነቂስ ወጥተው ለመትከል መዘጋጀታቸውን የደቡብ ኦሞ ዞን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
ነዋሪዎች ችግኞችን ተከላ ወደሚካሄድባቸው ቦታዎች የማጓጓዝ ሥራ እያጠናቀቁ ስለመሆናቸው ገለፀው ማለዳ 12፡00 ሰዓት ላይ ወጥተው እንደሚተክሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ታሪካዊ በሆነው ኢትዮጵያን እናልብሳት መርሐ ግብር ስለምንሳተፍ ደስተኞች ነን ያሉት አስተያየት ሰጪዎች የሚተከሉ ችግኞች ዘርፈብዙ ጠቀሜታው ያላቸው በመሆናቸው የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና የኢኮኖሚ አቅምን ለማሳደግ ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ ነው ብለዋል።
ለተከላ የሚሆኑ ቁሳቁሶችን በመያዝ ለመርሐ ግብሩ ያመች ዘንድ በአደረጃጀት ተለይታው እንደሚወጡም ነዋሪዎች ገልፀው መላው ኢትዮጵያዊያን ቃላችን ጠብቀን አሻራችንን እናሳርፍ ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
በደቡብ ኦሞ ዞን ነገ በአንድ ቀን ጀምበር 9 መቶ 13 ሺህ 46 ችግኞች በዞኑ በ10 ወረዳዎችና በሦስት ከተማ አስተዳድሮች ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል።
የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ጂንካ ቅርንጫፍ በወረዳዎች ተንቀሳቅሶ የችግኝ ዝግጅትና ለተከላው የተዘጋጁ ጉድጓዶችን ቅኝት አድርጓል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ