ነገ ለሚተከለው አንድ ቀን አረንዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ማለዳ በነቂስ ወጥተው ለመትከል መዘጋጀታቸውን የደቡብ ኦሞ ዞን ነዋሪዎች ገለፁ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 09/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ነገ ለሚተከለው አንድ ቀን አረንዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ማለዳ በነቂስ ወጥተው ለመትከል መዘጋጀታቸውን የደቡብ ኦሞ ዞን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
ነዋሪዎች ችግኞችን ተከላ ወደሚካሄድባቸው ቦታዎች የማጓጓዝ ሥራ እያጠናቀቁ ስለመሆናቸው ገለፀው ማለዳ 12፡00 ሰዓት ላይ ወጥተው እንደሚተክሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ታሪካዊ በሆነው ኢትዮጵያን እናልብሳት መርሐ ግብር ስለምንሳተፍ ደስተኞች ነን ያሉት አስተያየት ሰጪዎች የሚተከሉ ችግኞች ዘርፈብዙ ጠቀሜታው ያላቸው በመሆናቸው የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና የኢኮኖሚ አቅምን ለማሳደግ ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ ነው ብለዋል።
ለተከላ የሚሆኑ ቁሳቁሶችን በመያዝ ለመርሐ ግብሩ ያመች ዘንድ በአደረጃጀት ተለይታው እንደሚወጡም ነዋሪዎች ገልፀው መላው ኢትዮጵያዊያን ቃላችን ጠብቀን አሻራችንን እናሳርፍ ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
በደቡብ ኦሞ ዞን ነገ በአንድ ቀን ጀምበር 9 መቶ 13 ሺህ 46 ችግኞች በዞኑ በ10 ወረዳዎችና በሦስት ከተማ አስተዳድሮች ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል።
የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ጂንካ ቅርንጫፍ በወረዳዎች ተንቀሳቅሶ የችግኝ ዝግጅትና ለተከላው የተዘጋጁ ጉድጓዶችን ቅኝት አድርጓል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ውድና ውስን የሆነውን መሬት ያለብክነት ለመምራትና ለመጠቀም እየተሰራ ነው – የባስኬቶ ዞን አስተዳደር
በጎፋ ዞን ጋልማ ከተማ በ2019 በጀት ዓመት ከ18 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር መታቀዱ ተገለፀ
የሀድያ ብሔር የዘመን መለወጫ “ያሆዴ” በዓልን ለማክበር በቂ ዝግጅት መደረጉ ተገለጸ