በጉራጌ ዞን ከ175 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 09/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጉራጌ ዞን እምድብር ከተማ ከ175 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በክልሉ መንግስት እና በ“ዋንወሽ” የተገነባው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የደቡብ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው በተገኙበት ተመርቋል።
የንጹህ መጠጥ ውሃው ከ35 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገልጿል።
የንጹህ መጠጥ ውሃ ተገንብቶ መጠናቀቅ የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሚናው የጎላ ነው።
በውሃ ምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የደቡብ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳውን ጨምሮ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ግርማ፣ የዞን ከፍተኛ አመራሮች፣ የከተማው አመራሮች፣ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል፡፡
ምንጭ ፡ የጉራጌ ዞን ኮሙኒኬሽን መምሪያ

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር