በጉራጌ ዞን ከ175 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 09/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጉራጌ ዞን እምድብር ከተማ ከ175 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በክልሉ መንግስት እና በ“ዋንወሽ” የተገነባው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የደቡብ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው በተገኙበት ተመርቋል።
የንጹህ መጠጥ ውሃው ከ35 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገልጿል።
የንጹህ መጠጥ ውሃ ተገንብቶ መጠናቀቅ የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሚናው የጎላ ነው።
በውሃ ምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የደቡብ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳውን ጨምሮ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ግርማ፣ የዞን ከፍተኛ አመራሮች፣ የከተማው አመራሮች፣ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል፡፡
ምንጭ ፡ የጉራጌ ዞን ኮሙኒኬሽን መምሪያ

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ