በቤንች ሸኮ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዬን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 43 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደስራ መግባታቸው ተገለፀ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 05/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ)በቤንች ሸኮ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዬን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 43 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ተቀብሎ በተለያዩ የስራ ዘርፎች ማሰማራት መቻሉን የዞኑ ንግድና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታውቋል ።
ፕሮጀክቶቹ ከ1 ሺህ 560 በላይ ለሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የስራ ዕድል መፍጠር ችለዋል
በመምሪያው የኢንቨስትመንት ፖቴንሺያል ጥናት ፕሮሞሺን ፍቃድና መረጃ ቡድን መሪ አቶ ተስፋዬ ዳባ እንደተናገሩት በዞኑ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዬን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 43 ባለሀብቶች ተቀብሎ በተለያየ የኢንቨስትመንት ስራ ዘርፎች ማሰማራት መቻሉንተናግረዋል
በዞኑ የኢንቨስትመንት ፍቃድ ወስደው ወደስራ የገቡት እነዚህ ፕሮጀክቶች 10 በግብርና 27 በኢንዱስትሪና 5 በአገልግሎት ዘርፍ መሆናቸውንም አቶ ተስፋዬ አብራርተዋል
እነዚህም ፕሮጀክቶች በዞኑ ለሚኙ ከ1 ሺህ 562 ዜጐች ቋሚና ጊዜዊ የስራ እድል መፍጠር ችሏል ብለዋል፡፡
ዘጋቢ ፡ ጦያር ይማም ከሚዛን ጣቢያ

More Stories
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት
መደበኛ ባልሆነ መልኩ የሎተሪ ዕድል ሙከራን “ዕቁብ” በሚል ሽፋን በህገ-ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት አሳሰበ
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ