በቤንች ሸኮ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዬን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 43 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደስራ መግባታቸው ተገለፀ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 05/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ)በቤንች ሸኮ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዬን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 43 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ተቀብሎ በተለያዩ የስራ ዘርፎች ማሰማራት መቻሉን የዞኑ ንግድና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታውቋል ።
ፕሮጀክቶቹ ከ1 ሺህ 560 በላይ ለሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የስራ ዕድል መፍጠር ችለዋል
በመምሪያው የኢንቨስትመንት ፖቴንሺያል ጥናት ፕሮሞሺን ፍቃድና መረጃ ቡድን መሪ አቶ ተስፋዬ ዳባ እንደተናገሩት በዞኑ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዬን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 43 ባለሀብቶች ተቀብሎ በተለያየ የኢንቨስትመንት ስራ ዘርፎች ማሰማራት መቻሉንተናግረዋል
በዞኑ የኢንቨስትመንት ፍቃድ ወስደው ወደስራ የገቡት እነዚህ ፕሮጀክቶች 10 በግብርና 27 በኢንዱስትሪና 5 በአገልግሎት ዘርፍ መሆናቸውንም አቶ ተስፋዬ አብራርተዋል
እነዚህም ፕሮጀክቶች በዞኑ ለሚኙ ከ1 ሺህ 562 ዜጐች ቋሚና ጊዜዊ የስራ እድል መፍጠር ችሏል ብለዋል፡፡
ዘጋቢ ፡ ጦያር ይማም ከሚዛን ጣቢያ

More Stories
በቀቤና ልዩ ወረዳ የሚገነቡት የኢማም ሀሰን ኡንጀሞ ሆስፒታል እና የፈትሁዲን ላሉተ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ ፕሮጀክቶች የማህበረሰቡን የዘመናት የልማት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ መሆናቸውን ተገለፀ
በክልሉ ባለፉ 6 ወራት ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ