በጎፋ ዞን የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሄደ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 05/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጎፋ ዞን ከ120 ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሂዷል።
የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ጌትነት በጋሻው ወጣቶች ያላቸውን ዕምቅ አቅም ተጠቅመው በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዘርፍ በአካባቢው ልማት በንቃት በመሳተፍ ህብረተሰቡን ማገልገል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
ዞኑ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በሚከናወኑ ተግባራት ላይ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልፀው ተቋማት፣ ባለሀብቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
የዞኑ ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አወቀ ዓለሙ በበጋ ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሀ ግብር ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸውን ተግባራት መከናወናቸውን ገልፀዋል፡፡
በበጋ ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ69 ሺህ በላይ ወጣቶች የተሳታፉ ሲሆን 240 ሺህ የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ በማድረግ h63 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማዳን መቻሉን ተናግረዋል፡፡
በክረምት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት 120 ሺህ 576 ወጣቶችን በማሳተፍ 361 ሺ 728 የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱን አንስተዋል።
አክለውም በአገልግሎቱ 99 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ ለማደን ታቅዷል ብለዋል።
የመምሪያው ምክትል ኃላፊና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታደለ ታደሰ ለማህበረሰቡ ከፍተኛ ፈይዳ ባላቸው 11 የተለያዩ የስራ ዘርፎች ወጣቶቹ እንደሚሳተፉ ነው የገለጹት፡፡
በአረንጓዴ አሻራ፣ አረጋውያንን በመደገፍና ቤታቸውን መጠገን፣ በከተማ ጽዳት፣ በደም ልገሳ፣ በማጠናከሪያ ትምህርት፣ በጤናና በሌሎችም መስኮች ይሳተፋሉ ብለዋል።
ወጣት ተመስገን ኡባ እና ወጣት ማሩ ደባልቄ በጋራ እንዳሉት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ የህሊና እርካታ የሚሰጥ ተግባር በመሆኑ ወጣቶችን በማስተባበር በንቃት ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል ።
በዕለቱ አቅመ ደካማ የሆኑትን የወ/ሮ ሙተነ ሙሎ ቤት የማደስ ስራ ተሰርቷል።
ዘጋቢ፡ አይናለም ሰለሞን ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት
መደበኛ ባልሆነ መልኩ የሎተሪ ዕድል ሙከራን “ዕቁብ” በሚል ሽፋን በህገ-ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት አሳሰበ
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ