የቡሌ ወረዳ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት 26ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሄደ
በውይይቱ ከምክርቤቱ አባላት ወ/ሮ መብራቴ በየነና አቶ ሀይሉ ኢርባ የህዝብ እንደራሴ የሆነው ምክር ቤት በዓመት ውስጥ በዕቅድ በተቀመጠው መሰረት ጉባኤ በማካሄድ የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ መመለስ ሲገባ ወደኋላ መቅረት ይስተዋላል ብለዋል።
የምክር ቤቱ አባላት አክለውምበመንገድ፣ ውሃ፣ የምክርቤት ህንጻ ግንባታና ተጀምሮ በቆመው የቡሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ ዙሪያ ለምክርቤቱ ጥያቄ አንስተዋል።
የቡሌ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ ዋቆ ሞኮና የህብረተሰቡ የረዥም ግዜ ጥያቄ የነበረው የቡሌ ከተማ አስተዳደር ማስተር ፕላን በክልል ምክር ቤት የጸደቀውን ለምክር ቤቱ አባላት በባለሙያ ገለጻ ከተደረገበት በኋላ እንዲጸድቅ መደረጉን ዋና አፈጉባኤው ተናግረዋል።
የህብረተሰብ ጥያቄ የሆነው በመንገድ፣ ውሃ፣ የምክር ቤት ህንጻ ግንባታና ተጀምሮ በቆመው የቡሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ ዙሪያ ከወረዳው አስተዳዳሪ አቶ በራቆ በራሶ ምላሽ ተሰጥቶበታል።
የምክር ቤት ጉባኤ በዓመት ውስጥ መካሄድ የነበረበትን ያህል አልተካሄደም በሚል ከአባላቱ የቀረበው ቅሬታ ልክ ነው ያሉት የቡሌ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤው በዓመት ውስጥ 75 በመቶ ብቻ ጉባኤ ማካሄዳቸውን ተናግረዋል።
የህብረተሰቡ የረዥም ግዜ ጥያቄ የነበረው የቡሌ ከተማ አስተዳደር ማስተር ፕላን በክልል ምክር ቤት የጸደቀውን ለምክር ቤቱ አባላት በባለሙያ ገለጻ ከተደረገበት በኋላ እንዲጸድቅ መደረጉን ዋና አፈጉባኤው ተናግረዋል።
የህብረተሰብ ጥያቄ የሆነው በመንገድ፣ ውሃ፣ የምክር ቤት ህንጻ ግንባታና ተጀምሮ በቆመው የቡሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ ዙሪያ ከወረዳው አስተዳዳሪ አቶ በራቆ በራሶ ምላሽ ተሰጥቶበታል።
ዘጋቢ ፡ ውብሸት ካሣሁን ከፍስሐገነት ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ