የቡሌ ወረዳ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት 26ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሄደ
በውይይቱ ከምክርቤቱ አባላት ወ/ሮ መብራቴ በየነና አቶ ሀይሉ ኢርባ የህዝብ እንደራሴ የሆነው ምክር ቤት በዓመት ውስጥ በዕቅድ በተቀመጠው መሰረት ጉባኤ በማካሄድ የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ መመለስ ሲገባ ወደኋላ መቅረት ይስተዋላል ብለዋል።
የምክር ቤቱ አባላት አክለውምበመንገድ፣ ውሃ፣ የምክርቤት ህንጻ ግንባታና ተጀምሮ በቆመው የቡሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ ዙሪያ ለምክርቤቱ ጥያቄ አንስተዋል።
የቡሌ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ ዋቆ ሞኮና የህብረተሰቡ የረዥም ግዜ ጥያቄ የነበረው የቡሌ ከተማ አስተዳደር ማስተር ፕላን በክልል ምክር ቤት የጸደቀውን ለምክር ቤቱ አባላት በባለሙያ ገለጻ ከተደረገበት በኋላ እንዲጸድቅ መደረጉን ዋና አፈጉባኤው ተናግረዋል።
የህብረተሰብ ጥያቄ የሆነው በመንገድ፣ ውሃ፣ የምክር ቤት ህንጻ ግንባታና ተጀምሮ በቆመው የቡሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ ዙሪያ ከወረዳው አስተዳዳሪ አቶ በራቆ በራሶ ምላሽ ተሰጥቶበታል።
የምክር ቤት ጉባኤ በዓመት ውስጥ መካሄድ የነበረበትን ያህል አልተካሄደም በሚል ከአባላቱ የቀረበው ቅሬታ ልክ ነው ያሉት የቡሌ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤው በዓመት ውስጥ 75 በመቶ ብቻ ጉባኤ ማካሄዳቸውን ተናግረዋል።
የህብረተሰቡ የረዥም ግዜ ጥያቄ የነበረው የቡሌ ከተማ አስተዳደር ማስተር ፕላን በክልል ምክር ቤት የጸደቀውን ለምክር ቤቱ አባላት በባለሙያ ገለጻ ከተደረገበት በኋላ እንዲጸድቅ መደረጉን ዋና አፈጉባኤው ተናግረዋል።
የህብረተሰብ ጥያቄ የሆነው በመንገድ፣ ውሃ፣ የምክር ቤት ህንጻ ግንባታና ተጀምሮ በቆመው የቡሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ ዙሪያ ከወረዳው አስተዳዳሪ አቶ በራቆ በራሶ ምላሽ ተሰጥቶበታል።
ዘጋቢ ፡ ውብሸት ካሣሁን ከፍስሐገነት ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ