የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ለማሻሻል የተዘጋጀ የትምህርት ተሃድሶ ንቅናቄ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 03/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ “ትምህርት ለትውልድ” በሚል መሪ ቃል የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ለማሻሻል የተዘጋጀ የትምህርት ተሃድሶ ንቅናቄ በሀዋሳ እየተካሄደ ነው፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ፣ በኢፌዴሪ ከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ሚኒስትር በወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ የሚመራው የሚኒስትሮችና የሚኒስትር ዴኤታዎች ልዑክ፣ የሲዳማ ብሄራዊ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደ፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ በየነ በራሳ፣ የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎ መገኘታቸውን ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤት የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

More Stories
ውድና ውስን የሆነውን መሬት ያለብክነት ለመምራትና ለመጠቀም እየተሰራ ነው – የባስኬቶ ዞን አስተዳደር
በጎፋ ዞን ጋልማ ከተማ በ2019 በጀት ዓመት ከ18 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር መታቀዱ ተገለፀ
የሀድያ ብሔር የዘመን መለወጫ “ያሆዴ” በዓልን ለማክበር በቂ ዝግጅት መደረጉ ተገለጸ