በጥንት አባቶች ተጠብቆ የቆየውን የጌዴኦ ባህላዊ መልክአ ምድር ለቀጣይ ትውልድ ለማሸጋገር በትኩረት እየተሠራ ነው
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፍሎር ፕሮጀክት በዲላ ዩኒቨርሲቲ በመሬት አያያዝና አጠቃቀም ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት ስልጠና ሰጥቷል፡፡
በስልጠናው መክፈቻ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ልማት ቢሮ ምክትልና የደን ልማት ዘርፍ ኃላፊ ዮሴፍ ማሩ (ዶ/ር) እንደገለፁት የተሰጠው ስልጠና የጌዴኦ ባህላዊ መልክአ ምድርን በዘላቂነት በመጠበቅ ለቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍን መሰረት ያደረገ ነው፡፡
በስልጠናው በዲላ ዩኒቨርሲቲ በዘርፉ የተለያዩ ጥናትና ምርምር ያደረጉ ምሁራን፣ የዞንና የወረዳ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መሳተፋቸውን ኃላፊው ገልፀዋል፡፡
በጥንት አባቶች ተጠብቆ የቆየው የጌዴኦ ባህላዊ መልክአ ምድር ለቀጣይ ትውልድ ለማሸጋገር ቢሮው በትኩረት እየሠራ መሆኑን ኃላፊው አስታውቀዋል፡፡
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ሀብታሙ ተመስገን (ዶ/ር) እንደገለፁት፤ በማህበረሰብ አገልግሎት ዩኒቨርሲቲው ችግር ፈቺ ምርምሮችን በማድረግ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ነው፡፡
ምክትል ፕሬዚዳንቱ አክለውም፤ በዓለም የተመሰከረለትን ተራራማ አካባቢን ለእርሻ የመጠቀም የጌዴኦ ባህላዊ ጥበብ ለትውልድ ተሻጋሪ እንዲሆን ከባለድርሻዎች ጋር መነጋገር እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል፡፡
ውስን የተፈጥሮ ሀብት የሆነውን መሬትን በተቀናጀ መልኩ በዘላቂነት በመጠቀም ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ያደረጉት ውይይት መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፍሎር ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ አለምበጁ ክፍሌ አብራርተዋል፡፡
የቡናና የእንሰት ልማትን ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ የተፈጥሮን ደን መጠበቅ፣ መንከባከብ እና የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሰፍን በማድረግ ቀጣይነት ያለውን ልማት ለማስፋፋት ፕሮጀክቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሠራ ነው ሲሉም አቶ አለምበጁ ገልፀዋል፡፡
ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ዘሪሁን ዓለሙና ጴጥሮስ ሎሌ ከስልጠናው ያገኙትን ግንዛቤ ተግባር ላይ በማዋል የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ