በደቡብ ኦሞ ዞን አራት ወረዳዎች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ለተከሰተው የምግብ እጥረት የሰብአዊ ድጋፍ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ተካሄደ

በደቡብ ኦሞ ዞን አራት ወረዳዎች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ለተከሰተው የምግብ እጥረት የሰብአዊ ድጋፍ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ተካሄደ

ሀዋሳ፡ ሰኔ 22/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል  ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር በመተባበር በደቡብ ኦሞ ዞን አራት ወረዳዎች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ለተከሰተው የምግብ እጥረት የሰብአዊ ድጋፍ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር አካሂዷል።

ድጋፍ የሚደረግላቸው ዳሰነች፣ ሐመር፣ ኛንጋቶም እና ሰላማጎ ወረዳዎች ሲሆኑ ድጋፉ ከ259 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሆነ በመርሃ-ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ተገልጿል።

ድጋፉ የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ ካለበት መሰረታዊ ችግር እንዲወጣ ለማድረግ ያለመ ስለመሆኑ ተጠቁሟል።

በሚደረገው የሰብዓዊ እርዳታ በአራቱም ወረዳዎች ከ140 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ታውቋል።

በመርሃ-ግብሩ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል፣ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የአመራር አካላትን ጨምሮ  የደቡብ ክልልና የዞኑ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።

ዘጋቢ፡ ወንድወሰን ሽመል ከጂንካ ጣቢያችን