በደቡብ ኦሞ ዞን አራት ወረዳዎች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ለተከሰተው የምግብ እጥረት የሰብአዊ ድጋፍ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ተካሄደ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 22/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር በመተባበር በደቡብ ኦሞ ዞን አራት ወረዳዎች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ለተከሰተው የምግብ እጥረት የሰብአዊ ድጋፍ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር አካሂዷል።
ድጋፍ የሚደረግላቸው ዳሰነች፣ ሐመር፣ ኛንጋቶም እና ሰላማጎ ወረዳዎች ሲሆኑ ድጋፉ ከ259 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሆነ በመርሃ-ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ተገልጿል።
ድጋፉ የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ ካለበት መሰረታዊ ችግር እንዲወጣ ለማድረግ ያለመ ስለመሆኑ ተጠቁሟል።
በሚደረገው የሰብዓዊ እርዳታ በአራቱም ወረዳዎች ከ140 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ታውቋል።
በመርሃ-ግብሩ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል፣ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የአመራር አካላትን ጨምሮ የደቡብ ክልልና የዞኑ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ወንድወሰን ሽመል ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በመሎ ኮዛ ምርጫ ክልል በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምፅ መስጠት ተጀመረ
በካፋ ዞን ቢጣ ጌሻ ሞርጫ ክልል መራጮች ድምጽ መስጠት ጀምረዋል፡፡
ለተከታታይ 7 ምርጫዎች የተሳተፉ የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች