አስተዳደር ጽ/ቤቱ የ2017 ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2018 ዓ.ም መሪ ዕቅድ ላይ ውይይት አካሂዷል፡፡
በመድረኩ የጌዴኦ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ሮቤ እንደገለፁት፤ በ2017 በጀት ዓመት ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ ከባለድርሻዎች ጋር በቅንጅት ተግባራትን በመምራታቸው አበረታች ውጤት ከመመዝገቡ ባለፈ በርካታ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል፡፡
በአዲሱ በጀት ዓመት ያለውን ውስን ሀብት በተገቢው በመጠቀም ተጀምረው ያልተጠናቀቁ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ በትኩረት እየሰሩ መሆናቸውን አቶ ብርሃኑ አስታውቀዋል፡፡
ባለፈው በጀት አመት አፈፃፀም የተስተዋሉ ውስንነቶችን በማረም በስኬት የተነሱትን ይበልጥ በማጠናከር የዓመቱን ተግባር በመምራት ለተሻለ ውጤት ጥረት እንደሚያደርጉ የውይይቱ ተሳታፊዎች ሀሳብ አንስተዋል፡፡
የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ተገኝ ታደሰ፤ ባለፉት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች የተገኙ ስኬቶች በጋራ ጥረት የመጡ በመሆናቸው በየደረጃው የተሰጣችውን ኃላፊነት በተገቢው የተወጡ ባለድርሻዎችን አመስግነዋል፡፡
በዞኑ ያለውን እምቅ ፀጋ በአግባቡ በመጠቀም እንደ ሀገር ለዘመናት በድህነት የቆየንበት ዓመታትን በመረዳት በቁጭት ተግባራትን ማከናወንና ለለውጥ መትጋት እንደሚያስፈልግ አቶ ተገኝ ገልጸዋል።
በመድረኩ በ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም መነሻ የተሻለ አፈጻጸም ያላቸው መዋቅሮች እና ግለሰቦች ማበረታቻ ሽልማትና የዕውቅና ስነ-ስርዓት መርሃ ግብር እንዲሁም ረጅም ዓመታትን አገልግለው በጡረታ ለተሰናበቱ የሀገር ባለውለታዎች የክብር ሽኝት ተደርጓል።
ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ተገቢውን ትኩረት መስጠትና ተግቶ በመስራት ከድህነት መውጣት ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
ኢትዮጵያን ለዘመናት ከቆየችበት ቁስል ለማላቀቅ ባለፉት የለውጥ አመታት በርካታ ፖለቲካዊ ተግባራት ማከናወኑን መቻሉ ተገለጸ
ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎችን በመስራታቸው ዘርፈ ብዙ ጠቄሜታ ማግኘታቸውን የአርባምንጭ ፖሊ ቴክኒክና ሳታላይት ኮሌጅ ተማሪዎችና መምህራን ገለፁ