አቶ ጌታቸው ኬኒ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብሄረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ሆነው ተሾሙ
የክልሉ ምክር ቤት 3ኛ ዓመት 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ አካሂዷል።
ምክር ቤቱ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤው ላይ የክልሉ ብሄረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ አቶ ጌታቸው ኬንን ዋና አፈ ጉባኤ አድርጎ ሾሟል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ተወካይና ረዳት የመንግሥት ተጠሪ በአቶ በላይ ተሰማ አቅራቢነት አቶ ጌታቸው ኬኒ የክልሉ ብሄረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ሆነው እንዲሾሙ በምክር ቤት አባላት በሙሉ ድምፅ ፀድቋል።
በጉባኤው ላይ የክልሉ የመንግሥት ተወካዮች፣ የምክር ቤቱ አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ: አስቻለው አየለ – ከማሻ ጣቢያችን
More Stories
ባለፉት ጊዜያት በህዝብና በመንግስት መካከል ያለውን ግንኙነት ያጠናከሩ ተግባራት መከናወናቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ገለጸ
የኮሪደር ልማት ሥራ ከተማን ዉብ፣ ሳቢና ለነዋሪዎች ምቹ ከማድረግ ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች ሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን የዳዉሮ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ አስታወቀ
የተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት ዘርፍን በቤት ሙከራ በማስደገፍ ተማሪዎች የተሻለ ዕውቀት እንዲያገኙ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ