የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በሙሉ ፓኬጅ ተግባራዊ በማድረግ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ እንደሚገባ ተገለፀ
ሀዋሳ፣ ጥቅምት 01/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) “የግብርና እምርታ ለዘላቂ ከፍታ” በሚል መሪ ሀሳብ የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ የ2017/18 ሴክቶሪያል ጉባኤውን እያካሄደ ነው።
ግብርና ዘርፈ ብዙ የኢኮኖሚ መሠረት ነው ያሉት የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ማገሶ ማሾሌ ፤ በ2017 የምርት ዘመን የተመዘገቡ ምርጥ ተሞክሮችንና አፈጻጸሞችን በ2018 የምርት ዘመን በማጠናከር እንዲሁም የተስተዋሉ ጉድለቶችን በማረም ምርትና ምርታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል።
አክለውም ይህ ወቅት የመኸር ወቅት ጨርሰን ወደ በጋ መስኖ የምንሸጋገርበት በመሆኑ በ2018 በጋ መስኖ በስንዴና በሌሎች ሰብሎች እምርታ የምናስዘግብበት ነው ብለዋል።
የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር) እንዳሉት ፤ የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በሙሉ ፓኬጅ ተግባራዊ በማድረግ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸዋል ።
ግብርና የኢኮኖሚ ጀርባ አጥንት ነው ሲባል እንደሀገርና እንደየአካባቢው ምቹ የአየር ፀባይ በመጠቀም ምርታማነትን በማረጋገጥ ሕዝቡን ከተረጅነት ማላቀቅ ያስፈልጋል ብለዋል ዶ/ር ደምሴ ።
እንደጋሞ ዞን በእንስሳት እርባታ ፣ በፍራፍሬና በሌሎች ዘርፎች በ2017 የምርት ዘመን እምርታዎች እንደተመዘገቡ የገለጹት ዶ/ር ደምሴ በእጃችን ያሉ ፀጋዎችን ትኩረት ሰጥቶ ማስቀጠል እንደሚገባ አሳስበዋል ።
በመድረኩ የ2017 ምርት ዘመን የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ ሰነድ እየቀረበ ይገኛል።
ዘጋቢ: ሰለሞን አላሶ፦ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳዳር ጥያቄዎች በዘላቂነት እንዲመለሱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ገለፀ
መንግስት የደን ጭፍጨፋን በመከላከል የአየር ሚዛንን ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እስታውቀ