ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን !
የመስቀል በዓል በታላቅ ኃይማኖታዊ ስርዓት ከሚከበሩ የአደባባይ በዓላት መካከል አንዱና በዓለም አቀፉ የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም /UNESCO/ በዓለም የማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበ ልዩ በዓል ነው።
መስቀል በመደመር ዉስጥ ያለዉ ኃይልና ጉልበት የታየበት፣ በተለያዩ ባህሎችና ማህበረሰቦች ዉስጥ በድምቀት የሚከበር፤ ከኃይማኖታዊ ስርዓቱ በላይ የህብረ ብሄራዊ አንድነታችን መገለጫ የሆነ በዓል ነዉ።
በዓሉ ፍቅር የሚገለፅበትና አንድነት የሚያብብበት በዓል በመሆኑ በዓሉን ስናከብር እርስ በእርሳችን በመተሳሰብ፣ በመጠያየቅ፣ ከምንም በላይ ሰላማችንን አብዝተን በመጠበቅ እንዲሆን አደራ ለማለት እወዳለሁ።
በድጋሚ መልካም የመስቀል በዓል እንዲሆን እመኛለሁ።
አቶ ገ/መስቀል ጫላ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ
መስከረም 16/2018 ዓ.ም

More Stories
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ግማሽ አመት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ነው
መጪው ጠቅላላ ምርጫ ተአማኒና በህዝቡ ዘንድ ቅቡልነት ያለው እንዲሆን በልዩ ትኩረት እንደሚሠራ የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ደሣለኝ ገለፁ
የጌዴኦ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 28ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል