ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን !
የመስቀል በዓል በታላቅ ኃይማኖታዊ ስርዓት ከሚከበሩ የአደባባይ በዓላት መካከል አንዱና በዓለም አቀፉ የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም /UNESCO/ በዓለም የማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበ ልዩ በዓል ነው።
መስቀል በመደመር ዉስጥ ያለዉ ኃይልና ጉልበት የታየበት፣ በተለያዩ ባህሎችና ማህበረሰቦች ዉስጥ በድምቀት የሚከበር፤ ከኃይማኖታዊ ስርዓቱ በላይ የህብረ ብሄራዊ አንድነታችን መገለጫ የሆነ በዓል ነዉ።
በዓሉ ፍቅር የሚገለፅበትና አንድነት የሚያብብበት በዓል በመሆኑ በዓሉን ስናከብር እርስ በእርሳችን በመተሳሰብ፣ በመጠያየቅ፣ ከምንም በላይ ሰላማችንን አብዝተን በመጠበቅ እንዲሆን አደራ ለማለት እወዳለሁ።
በድጋሚ መልካም የመስቀል በዓል እንዲሆን እመኛለሁ።
አቶ ገ/መስቀል ጫላ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ
መስከረም 16/2018 ዓ.ም

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ