ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን !
የመስቀል በዓል በታላቅ ኃይማኖታዊ ስርዓት ከሚከበሩ የአደባባይ በዓላት መካከል አንዱና በዓለም አቀፉ የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም /UNESCO/ በዓለም የማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበ ልዩ በዓል ነው።
መስቀል በመደመር ዉስጥ ያለዉ ኃይልና ጉልበት የታየበት፣ በተለያዩ ባህሎችና ማህበረሰቦች ዉስጥ በድምቀት የሚከበር፤ ከኃይማኖታዊ ስርዓቱ በላይ የህብረ ብሄራዊ አንድነታችን መገለጫ የሆነ በዓል ነዉ።
በዓሉ ፍቅር የሚገለፅበትና አንድነት የሚያብብበት በዓል በመሆኑ በዓሉን ስናከብር እርስ በእርሳችን በመተሳሰብ፣ በመጠያየቅ፣ ከምንም በላይ ሰላማችንን አብዝተን በመጠበቅ እንዲሆን አደራ ለማለት እወዳለሁ።
በድጋሚ መልካም የመስቀል በዓል እንዲሆን እመኛለሁ።
አቶ ገ/መስቀል ጫላ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ
መስከረም 16/2018 ዓ.ም
More Stories
የተለያዩ የህክምና መድሀኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት መቻላቸውን በሚዛን አማን ከተማ በማህበረሰብ አቀፍ ፋርማሲ ሲገለገሉ ያገኘናቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ገለፁ
የየም ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “ሄቦ” በዓል በደማቅ ስነ ስርዓት በሣጃ ከተማ እየተከበረ ነው
በክረምት ወራት የታየውን ትጋት በበጋውም ለመድገም ቁርጠኞች መሆናቸውን በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ከተማ ወጣቶች ተናገሩ