የመስቀል ደመራ በዓል ስናከብር በአንድነትና በፍቅር ሊሆን ይገባል – የኮሬ ዞን ቤተክህነት
መስቀል ኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅሩን ለእኛ ያሳየበት በመሆኑ በአንድነትና በፍቅር ልናከብር ይገባናል ሲል የኮሬ ዞን ቤተ ክህነት አስታወቀ።
የኮሬ ዞን ቤተ ክህነት ስራ አስኪያጅ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታረቀኝ ሙቃ፥ መስቀል ደመራ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ትልቅ ቦታ የሚሰጠውና በድምቀት የሚከበር የአደባባይ በዓል መሆኑን ገልጸዋል።
ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሞቶ ፍቅሩን ለእኛ አሳይቷል ያሉት ቀሲስ ታረቀኝ እኛም በፍቅርና በአንድነት ከሁሉም ጋር እናከብራለን፤ ስናከብርም ቆይተናል ብለዋል።
በዓሉን ከሰንበት ተማሪዎች፣ ከካህናት፣ ከምዕመናንና አጠቃላይ ከማህበረሰቡ ጋር በድምቀት ለማክበር አስፈላጊ የሆኑ ዝግጅቶች መደረጋቸውን ጠቁመዋል።
ይህን በዓል በተለያዩ የባህል አልባሳት ደምቀን፣ ልዩነቶችን በማጥበብና አንድነትን በማጠናከር፣ ፍቅርን ለሌሎች በማካፈል ማክበር አለብን ሲሉ ተናግረዋል።
በመጨረሻም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል ።
ዘጋቢ: ለምለም ኦርሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ