መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር እንዳሻው ጣሰው መርቀው ከፈቱ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መዲና በሆሳዕና ከተማ የተመረቀው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር እንዳሻው ጣሰው፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የኘሮጀክቶች አስተባባሪ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ብርሀኑ ተስፋዬ፣ የክልሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዶክተር ዲላሞ ኦቶሬ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነው።
ማዕከሉ የዜጎችን እንግልት በማስቀረት ጊዜ፣ ወጪና ሀብት ከብክነት የሚታደግ ጥራት ያለው ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችል እንዲሁም የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ከማዘመን አንፃር የጎላ ፋይዳ እንዳለውም ተመላክቷል።
መሶብ በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ብቃት ያለው ተገልጋይን የሚመጥን አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ኢንሼቲቭ ነው።
በሆሳዕና ከተማ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጀመረው ይህ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ውስጥ 5 የፌደራል ተቋማት አገልግሎቶችን እንዲሁም 2 የክልል ተቋማት ከ20 በላይ የተለያዩ የአገልግሎት አይነቶችን ይሰጣል ተብሏል።
በማዕከሉ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት እንዲሁም የገቢዎች ቢሮ አገልግሎትን የሚሰጥ ሲሆን የኢሚግሬሽን፣ የንግድ ባንክ፣ ፖስታ አገልግሎት፣ ብሔራዊ መታወቂያ፣ ኢትዮ ቴሌኮም የመሳሰሉ የፌደራል ተቋማት አገልግሎትን በአንድ ስፍራ ማግኘት የሚያስችል ነው።
ቀጣይ ባሉ ጊዜያት አገልግሎቶቹን ወደ 60 የማሳደግ ዕቅድ መያዙም ታውቋል።
ዘጋቢ: አብደላ በድሩ
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር እንዳሻው ጣሰው መርቀው ከፈቱ

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ