ለሆሳዕና ማረሚያ ተቋም የህግ ታራሚዎች የተለያዩ ምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ
ሀዋሳ፡ መስከረም 14/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ሁሉ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ ህብረት ሥራ ማህበር ለሆሳዕና ማረሚያ ተቋም የህግ ታራሚዎች የተለያዩ ምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
የተቋሙ ኃላፊዎችና ታራሚዎች በበኩላቸው ለተደረገላቸው ድጋፍ አመስግነዋል።
የሁሉ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ የኅብረት ሥራ ማህበር የቦርድ አባል አቶ ሀብታሙ ታረቀኝ በድጋፉ ወቅት የሀዲያ ዘመን መለወጫ ያሆዴ በዓልን ከህግ ታራሚዎች ጋር መክበራቸው ደስታ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
ማህበሩ ከገንዘብ ቁጠባና ብድር ሥራ ባሻገር በሰብዓዊ ተግባራት በመሳተፍ በርካታ የድጋፍ ሥራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ ሃብታሙ፥ በሆሳዕና ማረሚያ ተቋም ለሚገኙ 230 የህግ ታራሚዎች የተለያዩ ምግብና ምግብ-ነክ ያልሆኑ ቁሳቁስ ማበርከቱን ገልፀዋል።
የሆሣዕና ማረሚያ ተቋም ኃላፊ ኮማንደር ዘውዱ ዱኖሮ በበኩላቸው የተለያዩ በጎ አድራጊዎችና ሃይማኖታዊ ተቋማት አንዲሁም ባለሀብቶች ሰፋፊ የድጋፍ ተግባራትን እያከናወኑ መሆናቸውን አንስተው፥ የሁሉ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ሥራ ማህበር ላደረገው መልካም ሥራ አመስግነዋል ።
የተቋሙ የህግ ታራሚዎች በሰጡት አስተያየት የሚደረጉ ድጋፎች ተገቢና የታራሚዎችን ችግር የሚያቃልል መሆኑን ገልፀው እገዛ ለደረጉ አካለትም ምስጋና አቅርበዋል።
ዘጋቢ: ኤልያስ ኤርሶ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ