የሀዲያ ዘመን መለወጫ የያሆዴ በዓል የዕርቅ፣የአብሮነት፣የይቅርታ፣ የመሻገሪያ እና ሌሎች በርካታ ባህላዊ ዕሴቶችን በውስጡ የያዘ ድንቅ ከኢትዮጵያ ባህሎች አንዱ ነው – የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
ሀዋሳ፣ መስከረም 13/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሀዲያ ብሄር ዘመን መለወጫ የያሆዴ በዓል በሀዲይ ነፈራ በድምቀት ተከብሯል።
በበዓሉ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እንደገለጹት የሀዲያ ዘመን መለወጫ የያሆዴ በዓል የዕርቅ፣የአብሮነት፣የይቅርታ፣ የመሻገሪያ እና ሌሎች በርካታ ባህላዊ ዕሴቶችን በውስጡ የያዘ ድንቅ ከኢትዮጵያ ባህሎች አንዱ ነው።
ኢትዮጵያ በህብረ ብሄራዊነት፣ ውብና ድንቅ ባህሎችና የተፈጥሮ ጸጋ የበለገች መሆኑን የገለጹት ዶክተር እንዳሻው ከእነዚህ አንዱ የሀዲያ ብሄር ዘመን መለወጫ የያሆዴ በዓል ነው ብለዋል።
የያሆዴ በዓል የዕርቅና የአብሮነት እንዲሁም ለልማት በአዲስ መልክ ቃላችንን የሚናድስበት ነው ብለዋል ዶክተር እንዳሻው።
ጽናትና ህብረት ለስኬት ማብቃቱን ተምረናል ያሉት ዶክተር እንዳሻው አሁንም ለሰላም፣ልማትና አንድነት መሰናክል የሚሆኑ ማነቆዎችን ለማጥፋት በአንድነት መቆም አለብን ብለዋል።
በገጠር ግብርና እና የኮሪደር ልማት አርሶአደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክሮ ይቀጥላሉ ያሉት ዶክተር እንዳሻው የሆሳዕና ከተማን ለነዋሪዎች እና እንግዶች ምቹ ለማድረግ እየተሰራ ያለው የኮሪደር ልማት ከግብ እንዲደርስ ህብረተሰቡ በተለይም ባለሀብቶች እያደረጉ ያለውን ተሳትፎ አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ሲሉም ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር እንዳሻው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።
ዘጋቢ:-ሳሙኤል መንታሞ ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ