6111 ok ለአርባ ምንጭ ስታድየም ግንባታ ባለ አራት ዲጅት የገቢ ማሰባሰቢያ ቁጥር ይፋ ተደረገ
ሀዋሳ: መስከረም 12/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ለአርባ ምንጭ ስታድየም ግንባታ ባለ አራት ዲጅት 6111 ok የገቢ ማሰባሰቢያ ቁጥር ይፋ መደረጉ ተገለፀ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ለአርባምንጭ አለም አቀፍ ስታዲዬም ግንባታ የገቢ ማሰባሰቢያ 6111 ባለ አራት ዲጅት ቁጥር ይፋ ሆኗል።
በአርባ ምንጭ ከተማ ለሚገነባው ስታዲዬም አሻራችንን እናኑር ለሚሉ የልማቱ ደጋፊዎች ” 6111 Ok ” በይፋ ማስጀመሪያ መርሃግብር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳድር በአቶ ጥላሁን ከበደ አማኝነት ይፋ ተደርግል።
6111 ok በማለት የአርባምንጭ ስታድየም ግንባታ የገቢ ማሰባሰቢያ ተሳትፎን ርእሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ መሪነት ስምፖዝየሙ ተሳታፊዎች ድጋፍ አደረግዋል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሸንካ በተገኙበት የተካሄደው ሲምፖዝየም፥ 6111 ok በማለት የሀብት ማሰባሰቢያ ተሳትፎ አድርገዋል።
በዚህም የስምፖዚየሙ ተሳታፊዎች በሙሉ የገቢ ማሰባሰቢያ ቁጥሩን በመጫን ድጋፍ አድርገዋል።
በመረሀግብሩ ላይ ርዕሰመስተዳድር ጥላሁን ከበደ፣ የባህልና ስፖርት ምንስቴር ወ/ሮ ሸዊት ሻንካን፣ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ(ዶ/ር)፣ የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን መንዛን (ዶ/ር) ጨምሮ ከፌዴራል፣ ክልል እና ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዞኖች እና ከጋሞ ዞን መዋቅሮች የተገኙ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ ፡ ገነት መኮንን- ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ