ማሽቃሮ ”ለሰላምና ለአብሮነት” በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ: መስከረም 12/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማሽቃሮ በዓልን ምክንያት በማድረግ ማሽቃሮ ”ለሰላምና ለአብሮነት” በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው።
የውይይቱ ዓላማ የቦንጋ ከተማ ዕድገት ባህላዊ እሴቶችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንዲሆንና የካፋ ባዮስፔር 15ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተገልጿል ።
በውይይቱ ላይ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ፤ የቀድሞ የካፋ ንጉስ ዘውድ ወደ ካፋ በመጣበት ወቅት በዓሉን ለማክበር የታደሙ አካላት እንኳን አደረሳችሁ ብለዋል።
የካፈቾ ዘመን መለወጫ በዓል በሚከበርበት ወቅት መልካም ተግባር ያከናወኑ አካላት የሚሞገሱበት መሆኑን አመላክተዋል ።
ቦንጋ ከተማ ከተቆረቆረ ረዥም ዘመናት ያስቆጠረ ቢሆንም በርካታ መሰረተ ልማት እጥረት ያለበት በመሆኑ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል።
ማሽቃሬ ባሮ የካፋ ተፈጥሮ ሀብትና ባህል ጋር የተቆራኘ እንደሆነም ተናግረዋል።
ማሽቃሬ ባሮ በዩኔስኮ እንዲመዘገብ የሚመለከታቸው አካላት ትኩረት እንዲያደርጉም ጠይቀዋል።
በፓናል ዉይይቱ በአፍሪካ የዩኔስኮ ተወካዮች፣ የናቡ አፍሪካ ኃላፊን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ነው።
ዘጋቢ : ሀብታሙ ኃይሌ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በመንግስት ድጋፍና በህብረተሰቡ ተሣትፎ የተገነባው ጤና ጣቢያ በጎፋ ዞን ደንባ ጎፋ ወረዳ ወይዴ ውርኪ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የሳውላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ወንጀልን የሚጸየፉ አምራች ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለፀ
በዳውሮ ዞን ገና ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳና የፓርቲ ምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃ ግብር ተካሄደ