“ለጎፋ ዞን አንድነትና ብልፅግና በጋራ እሮጣለሁ”በሚል መሪ ቃል የጎፋ ጋዜ ማስቃላ እና የኦይዳ ዮኦ ማስቃላ የጎዳና ላይ ሩጫ ተካሄደ
ሀዋሳ፡ መስከረም 12/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) “ለጎፋ ዞን አንድነትና ብልፅግና በጋራ እሮጣለሁ” በሚል መሪ ቃል የጎፋ ጋዜ ማስቃላ እና የኦይዳ ዮኦ ማስቃላ ምክንያት በማድረግ በጎፋ ዞን ታላቁ ሩጫ በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል።
የሩጫ ውድድሩ ኢትዮጵያን በዓለም አደባባይ ከፍ ብላ እንድትታይ ከሚያደርጓት ዘርፎች አንዱ ሲሆን የኢትዮጵያዊያን የጥንካሬና የአሸናፊነት መገለጫ የሆነው የሩጫ ውድድር “ለጎፋ ህዝብ አንድነትና እድገት እሮጣለሁ” በሚል መሪ ሃሳብ በሣውላ ከተማ ተካሂዷል።
በውድድሩ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚንስቴር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቦጋለ ፈይሳ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሶዶ ክላስተር አስተባባሪና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ውድድሩ የጎፋ ዞን አስተዳደር ከፋን ኢትዮጵያ ትሬዲንግ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሲሆን 8 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ነው።
ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደና የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በወ/ሮ አዱኛ አዛዥ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ
በረመዳን ወቅት የታየው ትጋትና አንድነት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተመላከተ
1ሺህ 447ኛ የኢድ አል ፈጥር በዓል በኮሬ ዞን ኬሌ ከተማ አሰተዳደር በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት ተከበረ