“ለጎፋ ዞን አንድነትና ብልፅግና በጋራ እሮጣለሁ”በሚል መሪ ቃል የጎፋ ጋዜ ማስቃላ እና የኦይዳ ዮኦ ማስቃላ የጎዳና ላይ ሩጫ ተካሄደ
ሀዋሳ፡ መስከረም 12/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) “ለጎፋ ዞን አንድነትና ብልፅግና በጋራ እሮጣለሁ” በሚል መሪ ቃል የጎፋ ጋዜ ማስቃላ እና የኦይዳ ዮኦ ማስቃላ ምክንያት በማድረግ በጎፋ ዞን ታላቁ ሩጫ በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል።
የሩጫ ውድድሩ ኢትዮጵያን በዓለም አደባባይ ከፍ ብላ እንድትታይ ከሚያደርጓት ዘርፎች አንዱ ሲሆን የኢትዮጵያዊያን የጥንካሬና የአሸናፊነት መገለጫ የሆነው የሩጫ ውድድር “ለጎፋ ህዝብ አንድነትና እድገት እሮጣለሁ” በሚል መሪ ሃሳብ በሣውላ ከተማ ተካሂዷል።
በውድድሩ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚንስቴር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቦጋለ ፈይሳ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሶዶ ክላስተር አስተባባሪና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ውድድሩ የጎፋ ዞን አስተዳደር ከፋን ኢትዮጵያ ትሬዲንግ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሲሆን 8 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ነው።
ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ