በኢፌደሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስተር ዶ/ር ተስፋዬ በልጅጌ የተመራ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ወደ ጎፋ ዞን ገቡ
በኢፌደሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ዶክተር ተስፋዬ በልጅጌ ጨምሮ፥ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባቴ፣ የፋን ኢትዮጵያ መስራችና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ፋንቱ ሜጊሶ እና የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ልዑካኑ ወደ ዞኑ ሲደርሱ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ ፣ የዞኑ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ጋሻለው እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ አመራሮች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ልዑካን ቡድኑ በዞኑ በሚኖራቸው ቆይታ “ለጎፋ ዞን አንድነትና ዕድገት እሮጣለሁ” በሚል መሪ ቃል በሚደረገው ታላቁ ሩጫ እንደሚሳተፉና የጎፋ ጋዜ ማስቃላ እና የኦይዳ ዮኦ ማስቃላ በዓልን ለማክበር መሆኑ ተገልጿል።
ዘጋቢ: አይናለም ሰለሞን – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ