በኢፌደሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስተር ዶ/ር ተስፋዬ በልጅጌ የተመራ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ወደ ጎፋ ዞን ገቡ
በኢፌደሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ዶክተር ተስፋዬ በልጅጌ ጨምሮ፥ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባቴ፣ የፋን ኢትዮጵያ መስራችና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ፋንቱ ሜጊሶ እና የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ልዑካኑ ወደ ዞኑ ሲደርሱ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ ፣ የዞኑ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ጋሻለው እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ አመራሮች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ልዑካን ቡድኑ በዞኑ በሚኖራቸው ቆይታ “ለጎፋ ዞን አንድነትና ዕድገት እሮጣለሁ” በሚል መሪ ቃል በሚደረገው ታላቁ ሩጫ እንደሚሳተፉና የጎፋ ጋዜ ማስቃላ እና የኦይዳ ዮኦ ማስቃላ በዓልን ለማክበር መሆኑ ተገልጿል።
ዘጋቢ: አይናለም ሰለሞን – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
በመንግስት ድጋፍና በህብረተሰቡ ተሣትፎ የተገነባው ጤና ጣቢያ በጎፋ ዞን ደንባ ጎፋ ወረዳ ወይዴ ውርኪ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የሳውላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ወንጀልን የሚጸየፉ አምራች ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለፀ
በዳውሮ ዞን ገና ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳና የፓርቲ ምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃ ግብር ተካሄደ