የህዝበ ውሳኔውን አጠቃላይ ውጤት በትዕግስት እንጠብቃለን – መራጮች

የህዝበ ውሳኔውን አጠቃላይ ውጤት በትዕግስት እንጠብቃለን – መራጮች

ሀዋሳ: ሰኔ 13/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በወላይታ ዞን የተካሄደው ድጋሚ ህዝበ ውሳኔ አጠቃላይ የድምፅ ውጤት በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ  እስኪገለፅ ድረስ በትዕግስት መጠበቅ እንደሚገባ በሶዶ ከተማ በህዝበ ውሳኔው የተሳተፉ መራጮች ተናገሩ::

በሶዶ ከተማ የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዚያዊ ውጤት ይፋ ማድረጋቸውን ተከትሎ መራጮች ጊዚያዊ ውጤቱን እየተመለከቱ ይገኛሉ::

ጊዚያዊ ውጤቱን ሲመለከቱ ደሬቴድ ያነጋገራቸው መራጮች ምርጫው በሠላም በመጠናቀቁ ደስተኞች ነን ብለዋል::

በምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደት ተጠናቆ ጊዚያዊ ውጤቶችም መለጠፋቸው አስፈፃሚዎች ሥራቸውን በተያዘላቸው የጊዜ ሰለዳ መሠረት እያከናውኑ እንደሚገኙ የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል::

በጊዚያ ውጤቱ ደስተኞች ነን ያሉት መራጮቹ በቀጣይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አጠቃላይ የምርጫውን ውጤት ይፋ እስከሚያደርግ ድረስ በትዕግስት መጠበቅና ውጤቱንም በፀጋ ለመቀበል ዝግጁ መሆን ያስፈልጋል ብለዋል::

ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ