የህዝበ ውሳኔውን አጠቃላይ ውጤት በትዕግስት እንጠብቃለን – መራጮች
ሀዋሳ: ሰኔ 13/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በወላይታ ዞን የተካሄደው ድጋሚ ህዝበ ውሳኔ አጠቃላይ የድምፅ ውጤት በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እስኪገለፅ ድረስ በትዕግስት መጠበቅ እንደሚገባ በሶዶ ከተማ በህዝበ ውሳኔው የተሳተፉ መራጮች ተናገሩ::
በሶዶ ከተማ የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዚያዊ ውጤት ይፋ ማድረጋቸውን ተከትሎ መራጮች ጊዚያዊ ውጤቱን እየተመለከቱ ይገኛሉ::
ጊዚያዊ ውጤቱን ሲመለከቱ ደሬቴድ ያነጋገራቸው መራጮች ምርጫው በሠላም በመጠናቀቁ ደስተኞች ነን ብለዋል::
በምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደት ተጠናቆ ጊዚያዊ ውጤቶችም መለጠፋቸው አስፈፃሚዎች ሥራቸውን በተያዘላቸው የጊዜ ሰለዳ መሠረት እያከናውኑ እንደሚገኙ የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል::
በጊዚያ ውጤቱ ደስተኞች ነን ያሉት መራጮቹ በቀጣይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አጠቃላይ የምርጫውን ውጤት ይፋ እስከሚያደርግ ድረስ በትዕግስት መጠበቅና ውጤቱንም በፀጋ ለመቀበል ዝግጁ መሆን ያስፈልጋል ብለዋል::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ
More Stories
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ
“የብልጽግና ጉዞአችንና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ ክልላዊ የንግዱ ማሕበረሰብ ማጠቃለያ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው
በዞኑ ኩረጃን የሚፀየፍ ብቁና ተወዳዳሪ ትውልድ ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ