የህዝበ ውሳኔውን አጠቃላይ ውጤት በትዕግስት እንጠብቃለን – መራጮች
ሀዋሳ: ሰኔ 13/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በወላይታ ዞን የተካሄደው ድጋሚ ህዝበ ውሳኔ አጠቃላይ የድምፅ ውጤት በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እስኪገለፅ ድረስ በትዕግስት መጠበቅ እንደሚገባ በሶዶ ከተማ በህዝበ ውሳኔው የተሳተፉ መራጮች ተናገሩ::
በሶዶ ከተማ የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዚያዊ ውጤት ይፋ ማድረጋቸውን ተከትሎ መራጮች ጊዚያዊ ውጤቱን እየተመለከቱ ይገኛሉ::
ጊዚያዊ ውጤቱን ሲመለከቱ ደሬቴድ ያነጋገራቸው መራጮች ምርጫው በሠላም በመጠናቀቁ ደስተኞች ነን ብለዋል::
በምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደት ተጠናቆ ጊዚያዊ ውጤቶችም መለጠፋቸው አስፈፃሚዎች ሥራቸውን በተያዘላቸው የጊዜ ሰለዳ መሠረት እያከናውኑ እንደሚገኙ የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል::
በጊዚያ ውጤቱ ደስተኞች ነን ያሉት መራጮቹ በቀጣይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አጠቃላይ የምርጫውን ውጤት ይፋ እስከሚያደርግ ድረስ በትዕግስት መጠበቅና ውጤቱንም በፀጋ ለመቀበል ዝግጁ መሆን ያስፈልጋል ብለዋል::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ
More Stories
”የምንተክላቸው ችግኞች ለትውልድ ተሻጋሪ ትሩፋትን የሚያስገኙ ናቸው” – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ
ከማረምና ማነጽ ጎን ለጎን የሀገሪቱን አረንጓዴ ልማት እስትራቴጂን ለማሳካት ሚናውን እንደሚወጣ የጂንካ ማረሚያ ተቋም አስታወቀ
“በክልሉ ባለፉት አመታት የተተከሉ ችግኞች ለኢኮኖሚ እና የስራ ዕድል ፈጠራ ምንጭ ሆነዋል” ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ