የህዝበ ውሳኔውን አጠቃላይ ውጤት በትዕግስት እንጠብቃለን – መራጮች
ሀዋሳ: ሰኔ 13/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በወላይታ ዞን የተካሄደው ድጋሚ ህዝበ ውሳኔ አጠቃላይ የድምፅ ውጤት በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እስኪገለፅ ድረስ በትዕግስት መጠበቅ እንደሚገባ በሶዶ ከተማ በህዝበ ውሳኔው የተሳተፉ መራጮች ተናገሩ::
በሶዶ ከተማ የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዚያዊ ውጤት ይፋ ማድረጋቸውን ተከትሎ መራጮች ጊዚያዊ ውጤቱን እየተመለከቱ ይገኛሉ::
ጊዚያዊ ውጤቱን ሲመለከቱ ደሬቴድ ያነጋገራቸው መራጮች ምርጫው በሠላም በመጠናቀቁ ደስተኞች ነን ብለዋል::
በምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደት ተጠናቆ ጊዚያዊ ውጤቶችም መለጠፋቸው አስፈፃሚዎች ሥራቸውን በተያዘላቸው የጊዜ ሰለዳ መሠረት እያከናውኑ እንደሚገኙ የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል::
በጊዚያ ውጤቱ ደስተኞች ነን ያሉት መራጮቹ በቀጣይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አጠቃላይ የምርጫውን ውጤት ይፋ እስከሚያደርግ ድረስ በትዕግስት መጠበቅና ውጤቱንም በፀጋ ለመቀበል ዝግጁ መሆን ያስፈልጋል ብለዋል::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ