በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ በተደጋጋሚ በአርብቶና አርሶ አደር መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በሠላማዊ መንገድ መጨረስ የሚያስችል ባህላዊ ዕርቀ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል
ሀዋሳ: ሰኔ 13/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ በተደጋጋሚ በአርብቶና አርሶ አደር መሐል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በሠላማዊ መንገድ መጨረስ የሚያስችል ባህላዊ ዕርቀ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል።
በሥነ ሥርዓቱ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ንጋቱ ዳንሳን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
በሳላማጎ ወረዳ ሙርሲ፣ ቦዲ፣ ዲሜና ባጫ ብሔረሰቦች በጋራ ተቻችለውና ተፈቃቅረው የሚኖሩ ሲሆን አልፎ አልፎ በጥቂት ምክንያቶች አለመግባባት ተፈጥሮ የንብረት ውድመትና ለሰው ልጅ ሞት መንስኤ ሲሆን ይስተዋላል።
ይህ ደግሞ በተደጋጋሚ የሚከሰት መሆኑ በአካባቢው ዘላቂ ዕርቀ ሠላም በማስፈለጉ ሁሉ አቀፍ ባህላዊ ዕርቀ ሠላም ሥነ ሥርዓት ነው እየተካሄደ የሚገኘው።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ