በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ በተደጋጋሚ በአርብቶና አርሶ አደር መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በሠላማዊ መንገድ መጨረስ የሚያስችል ባህላዊ ዕርቀ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል
ሀዋሳ: ሰኔ 13/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ በተደጋጋሚ በአርብቶና አርሶ አደር መሐል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በሠላማዊ መንገድ መጨረስ የሚያስችል ባህላዊ ዕርቀ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል።
በሥነ ሥርዓቱ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ንጋቱ ዳንሳን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
በሳላማጎ ወረዳ ሙርሲ፣ ቦዲ፣ ዲሜና ባጫ ብሔረሰቦች በጋራ ተቻችለውና ተፈቃቅረው የሚኖሩ ሲሆን አልፎ አልፎ በጥቂት ምክንያቶች አለመግባባት ተፈጥሮ የንብረት ውድመትና ለሰው ልጅ ሞት መንስኤ ሲሆን ይስተዋላል።
ይህ ደግሞ በተደጋጋሚ የሚከሰት መሆኑ በአካባቢው ዘላቂ ዕርቀ ሠላም በማስፈለጉ ሁሉ አቀፍ ባህላዊ ዕርቀ ሠላም ሥነ ሥርዓት ነው እየተካሄደ የሚገኘው።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ
“የብልጽግና ጉዞአችንና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ ክልላዊ የንግዱ ማሕበረሰብ ማጠቃለያ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው
በዞኑ ኩረጃን የሚፀየፍ ብቁና ተወዳዳሪ ትውልድ ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ