በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ በተደጋጋሚ በአርብቶና አርሶ አደር መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በሠላማዊ መንገድ መጨረስ የሚያስችል ባህላዊ ዕርቀ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል
ሀዋሳ: ሰኔ 13/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ በተደጋጋሚ በአርብቶና አርሶ አደር መሐል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በሠላማዊ መንገድ መጨረስ የሚያስችል ባህላዊ ዕርቀ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል።
በሥነ ሥርዓቱ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ንጋቱ ዳንሳን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
በሳላማጎ ወረዳ ሙርሲ፣ ቦዲ፣ ዲሜና ባጫ ብሔረሰቦች በጋራ ተቻችለውና ተፈቃቅረው የሚኖሩ ሲሆን አልፎ አልፎ በጥቂት ምክንያቶች አለመግባባት ተፈጥሮ የንብረት ውድመትና ለሰው ልጅ ሞት መንስኤ ሲሆን ይስተዋላል።
ይህ ደግሞ በተደጋጋሚ የሚከሰት መሆኑ በአካባቢው ዘላቂ ዕርቀ ሠላም በማስፈለጉ ሁሉ አቀፍ ባህላዊ ዕርቀ ሠላም ሥነ ሥርዓት ነው እየተካሄደ የሚገኘው።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በቀቤና ልዩ ወረዳ የሚገነቡት የኢማም ሀሰን ኡንጀሞ ሆስፒታል እና የፈትሁዲን ላሉተ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ ፕሮጀክቶች የማህበረሰቡን የዘመናት የልማት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ መሆናቸውን ተገለፀ
በክልሉ ባለፉ 6 ወራት ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ