በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ በተደጋጋሚ በአርብቶና አርሶ አደር መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በሠላማዊ መንገድ መጨረስ የሚያስችል ባህላዊ ዕርቀ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል
ሀዋሳ: ሰኔ 13/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ በተደጋጋሚ በአርብቶና አርሶ አደር መሐል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በሠላማዊ መንገድ መጨረስ የሚያስችል ባህላዊ ዕርቀ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል።
በሥነ ሥርዓቱ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ንጋቱ ዳንሳን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
በሳላማጎ ወረዳ ሙርሲ፣ ቦዲ፣ ዲሜና ባጫ ብሔረሰቦች በጋራ ተቻችለውና ተፈቃቅረው የሚኖሩ ሲሆን አልፎ አልፎ በጥቂት ምክንያቶች አለመግባባት ተፈጥሮ የንብረት ውድመትና ለሰው ልጅ ሞት መንስኤ ሲሆን ይስተዋላል።
ይህ ደግሞ በተደጋጋሚ የሚከሰት መሆኑ በአካባቢው ዘላቂ ዕርቀ ሠላም በማስፈለጉ ሁሉ አቀፍ ባህላዊ ዕርቀ ሠላም ሥነ ሥርዓት ነው እየተካሄደ የሚገኘው።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ
በሁሉም ዘርፎች እንደሀገር አመርቂ ውጤቶች እየተዘመገቡ ነው – የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓትን በማዘመን የመረጃ ታማኝነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ