በፍትህ ተቋማት ግልፀኝነትና ተጠያቂነትን ማስፈን ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ተባለ
ሀዋሳ፣ መስከረም 08/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በኮሬ ዞን ፍ/ቤቶችና የፍትህ ተቋማት ሪፎርም ፍኖተ ካርታ አፈጻጸም መመሪያ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ ተካሂዷል ።
የኮሬ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ አካላት በቀለ፤ በፍትህ ስርዓቱ ተፈፃሚነት ላይ የፍ/ቤቶች ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ኃላፊነታቸውን በሚገባ መወጣት አለባቸው ብለዋል።
ከጀመረ ሁለት ዓመታትን ያስቆጠረው የፍኖተ ካርታው ሪፎርም በየጊዜዉ በስትሪንግ ኮሚቴ እየተገመገመ መቆየቱን ጠቁመው የተጀመረውን ሪፎርም የማጥራት ተግባራትን ለማከናወን መድረኩ እንዳስፈለገ ነው የገለፁት ።
የኮሬ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አስታረቀኝ አንዳባ መንግስት በፍትህ ተቋማት ላይ የሚስተዋሉትን ክፍተቶች ለመሙላት ሪፎርም ቀርጾ በመስራት ላይ ይገኛል ነው ያሉት ።
በፍትህ ተቋማት የዳኝነት ግልፀኝነትና ተጠያያቅነት ማስፈን ፣ በሰብዓዊ መብት አያያዝ ማስተካከልና አገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት ከሁሉም ባለድርሻዎች ይጠበቃል ብለዋል።
በምክክር መድኩ ላይ የፍ/ቤቶችና የፍትህ ተቋማትን አፈጻጸም ለተሳታፊዎች ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል ።
በፍትህ ዘርፉ የተገልጋይ እርካታ ፣ የፍትህ ተደራሽነት፣ ባህላዊ የዳኝነት ሥርዓትን ማጠናከር፣ ወንጀልን መከላከል ትኩረት ተሰጥቶባቸው ከተከናወኑ ተግባራት መካከል ተጠቃሾች እንደሆኑ በቀረበው ሰነድ ላይ ተመላክቷል።
የመድረኩ ተሳታፊዎችም ሪፎረሙ ከተጀመረ ወዲህ በፍትህ ተቋማት ላይ ለውጦች በመታየት ላይ እንዳሉ ጠቁመው በቀጣይ ለፍትህ ዘርፉ እንቅፋት የሚሆኑትን በማጥራት ሁላችንም የድርሻችንን መወጣት አለብን ሲሉ ተናግረዋል ።
ዘጋቢ : ለምለም ኦርሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ