በወላይታ ዞን ድጋሚ የሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ሠላማዊ እንዲሆን በቂ ዝግጅት ተደርጓል – አቶ ተስፋዬ ጎአ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 10/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በወላይታ ዞን ድጋሚ የሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ሠላማዊ እንዲሆን በቂ ዝግጅት መደረጉን የወላይታ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ጎአ ገለፁ::
አቶ ተስፋዬ በተለይም ለደሬቴድ እንደተናገሩት በወላይታ ዞን ዳግም በሚካሄደው የህዝበ ውሳኔ ምርጫ ላይ ህዝቡ ዴሞክራሲያዊ የመምረጥ መብቱን ተጠቅሞ በነቂስ መሳተፍ እንዲችል የፀጥታው መዋቅር የሚጠበቅበትን ለመወጣት ዝግጅቱን አጠናቋል ነው ያሉት::
በዕለቱ ህዝቡ ዴሞክራሲያዊ መብቱን እንዳይጠቀም በተለያየ መንገድ የማደናቀፍ ሥራ ማድረግ የሚፈልጉ አካላት ካሉ ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ለምርጫው ሠላማዊነት፣ ፍትሀዊነት እና ዴሞክራሲያዊነት የድርሻውን እንዲያበረክት ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ
More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጌዴኦ ዞን በ2017 ዓ.ም በመኸር እርሻ ከ24 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለመሸፈን አቅዶ እየሠራ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ
”የምንተክላቸው ችግኞች ለትውልድ ተሻጋሪ ትሩፋትን የሚያስገኙ ናቸው” – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ
ከማረምና ማነጽ ጎን ለጎን የሀገሪቱን አረንጓዴ ልማት እስትራቴጂን ለማሳካት ሚናውን እንደሚወጣ የጂንካ ማረሚያ ተቋም አስታወቀ