በወላይታ ዞን ድጋሚ የሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ሠላማዊ እንዲሆን በቂ ዝግጅት ተደርጓል – አቶ ተስፋዬ ጎአ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 10/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በወላይታ ዞን ድጋሚ የሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ሠላማዊ እንዲሆን በቂ ዝግጅት መደረጉን የወላይታ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ጎአ ገለፁ::
አቶ ተስፋዬ በተለይም ለደሬቴድ እንደተናገሩት በወላይታ ዞን ዳግም በሚካሄደው የህዝበ ውሳኔ ምርጫ ላይ ህዝቡ ዴሞክራሲያዊ የመምረጥ መብቱን ተጠቅሞ በነቂስ መሳተፍ እንዲችል የፀጥታው መዋቅር የሚጠበቅበትን ለመወጣት ዝግጅቱን አጠናቋል ነው ያሉት::
በዕለቱ ህዝቡ ዴሞክራሲያዊ መብቱን እንዳይጠቀም በተለያየ መንገድ የማደናቀፍ ሥራ ማድረግ የሚፈልጉ አካላት ካሉ ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ለምርጫው ሠላማዊነት፣ ፍትሀዊነት እና ዴሞክራሲያዊነት የድርሻውን እንዲያበረክት ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ
More Stories
የማታ 1፡00 ዜና 24፤ ሀዋሳ፡ ጥቅምት 04/2018 ዓ.ም
ጃፓን በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ብራዚልን አሸነፈች
ከተሞች በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዘው አገልግሎት መሥጠታቸው የተገልጋይና የአገልጋይ ግንኙነት ጤናማና እርካታ የተሞላበት እንዲሆን የሚያስችል መሆኑ ተገለጸ