በወላይታ ዞን ድጋሚ የሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ሠላማዊ እንዲሆን በቂ ዝግጅት ተደርጓል – አቶ ተስፋዬ ጎአ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 10/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በወላይታ ዞን ድጋሚ የሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ሠላማዊ እንዲሆን በቂ ዝግጅት መደረጉን የወላይታ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ጎአ ገለፁ::
አቶ ተስፋዬ በተለይም ለደሬቴድ እንደተናገሩት በወላይታ ዞን ዳግም በሚካሄደው የህዝበ ውሳኔ ምርጫ ላይ ህዝቡ ዴሞክራሲያዊ የመምረጥ መብቱን ተጠቅሞ በነቂስ መሳተፍ እንዲችል የፀጥታው መዋቅር የሚጠበቅበትን ለመወጣት ዝግጅቱን አጠናቋል ነው ያሉት::
በዕለቱ ህዝቡ ዴሞክራሲያዊ መብቱን እንዳይጠቀም በተለያየ መንገድ የማደናቀፍ ሥራ ማድረግ የሚፈልጉ አካላት ካሉ ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ለምርጫው ሠላማዊነት፣ ፍትሀዊነት እና ዴሞክራሲያዊነት የድርሻውን እንዲያበረክት ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ

More Stories
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ