በሀዲያ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት አለፈ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሀዲያ ዞን ምሻ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለጸ::
መነሻውን ከሆሳዕና በማድረግ ወደ ጊቤ ወረዳ ሶዳ ኦሞጮራ ሰው ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ኮድ 3 የሰሌዳ ቁጥር 19027 ሚኒባስ ተሽከርካሪ ላይ የመገልበጥ አደጋ መድረሱን የምሻ ወረዳ ፖሊስ ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ሆሳዕና ቅርንጫፍ ገልጿል።
አደጋው የደረሰው በሀዲያ ዞን ምሻ ወረዳ ሲኮ ቀበሌ ልዩ ስሙ ኤጌደ ተብሎ በሚጠራበት አካባቢ ከቀኑ 5፡30 መሆኑ ተመላክቷል::
ሌሎች ከባድ አደጋ የደረሰባቸው አስር ሰዎች በምሻ ወረዳና በጊቤ ወረዳ አምቡላንሶች ታግዘው ወደ ሆሳዕና ንግስት ኢሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለህክምና መላካቸውን የወረዳው ማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ዘርፍ ሀላፊ ዋና ኢንስፔክተር ተስፋዬ ባህሩ ገልጸዋል።
ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ሆሳዕና ጣቢያ መረጃውን በስልክ ያደረሱት ዋና ኢንስፔክተር ተስፋዬ ባህሩ፤ በአደጋው የሦስት ሰዎች ህይወት ወዲያው እንዳለፈና የአንድ ሰው ግን በሞርሲጦ ጤና ጣቢያ ህክምና እየተደረገለት ሳለ ህይወቱ ማለፉን ጠቁመው፤ የአደጋው መንስኤ እየተጠራ መሆኑንም ነው የተናገሩት::
ዘጋቢ: አለቃል ደስታ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ መንግሥት ወቅቱን የጠበቀና ጥራት ያለው ውሳኔ እንዲሰጥ የሚያስችል መሆኑን በኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት የአርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገለፀ
የጎርፍ መውረጃ ቦይ አለመሠራት በቤት ንብረታቸው ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን በከምባታ ዞን የዳምቦያ ከተማ አስተዳደር የ02 ቀበሌ ነዋሪዎች ገለጹ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የፕላን መሰረተ ልማት እና የመንግስት ሀብት አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአርባ ምንጭ ከተማ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ግማሽ አመት የተከናወኑ ተግባራትን የመስክ ምልከታ አደረገ