በሀዲያ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት አለፈ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሀዲያ ዞን ምሻ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለጸ::
መነሻውን ከሆሳዕና በማድረግ ወደ ጊቤ ወረዳ ሶዳ ኦሞጮራ ሰው ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ኮድ 3 የሰሌዳ ቁጥር 19027 ሚኒባስ ተሽከርካሪ ላይ የመገልበጥ አደጋ መድረሱን የምሻ ወረዳ ፖሊስ ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ሆሳዕና ቅርንጫፍ ገልጿል።
አደጋው የደረሰው በሀዲያ ዞን ምሻ ወረዳ ሲኮ ቀበሌ ልዩ ስሙ ኤጌደ ተብሎ በሚጠራበት አካባቢ ከቀኑ 5፡30 መሆኑ ተመላክቷል::
ሌሎች ከባድ አደጋ የደረሰባቸው አስር ሰዎች በምሻ ወረዳና በጊቤ ወረዳ አምቡላንሶች ታግዘው ወደ ሆሳዕና ንግስት ኢሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለህክምና መላካቸውን የወረዳው ማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ዘርፍ ሀላፊ ዋና ኢንስፔክተር ተስፋዬ ባህሩ ገልጸዋል።
ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ሆሳዕና ጣቢያ መረጃውን በስልክ ያደረሱት ዋና ኢንስፔክተር ተስፋዬ ባህሩ፤ በአደጋው የሦስት ሰዎች ህይወት ወዲያው እንዳለፈና የአንድ ሰው ግን በሞርሲጦ ጤና ጣቢያ ህክምና እየተደረገለት ሳለ ህይወቱ ማለፉን ጠቁመው፤ የአደጋው መንስኤ እየተጠራ መሆኑንም ነው የተናገሩት::
ዘጋቢ: አለቃል ደስታ – ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
”ሠላምን ማፅናት ለክልሉ ሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት ጉባኤ በሆሳዕና ከተማ መካሔድ ጀመረ
የክረምት ዝናብን ተከትሎ ጎርፍ እና መሰል አደጋዎች በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት እንዳያስከትሉ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ
በደቡብ ኦሞ ዞን ማሌ ወረዳ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሀ-ግብር ቤት የተገነባላቸዉ አካላት መደሰታቸውን ገለፁ