ፍትሀዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራትን ለማሳደግ በትኩረት መስራት ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 21/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትሀዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራትን ለማሳደግ በትኩረት መሰራት እንደሚገባ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ዓመታዊ የዕቅድ አፈፃፀምና ግምገማ መድረክ በሶዶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የጤና ፕሮግራም ዘርፍ ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ በቀጣይ የልማት ፕሮግራሞች በይበልጥ ጥራቱ የተጠበቀ ከማድረግ ረገድ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ኤካ በበኩላቸው ባለፈው በጀት ዓመት በበሽታ መከላከል የእናቶችንና የሕፃናትን ሞት በመቀነስ ረገድ ጠንካራ ተግባራት የተከናወኑ ሲሆን በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።
ዘጋቢ: ፀሐይ ጎበና – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ