ፍትሀዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራትን ለማሳደግ በትኩረት መስራት ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 21/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትሀዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራትን ለማሳደግ በትኩረት መሰራት እንደሚገባ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ዓመታዊ የዕቅድ አፈፃፀምና ግምገማ መድረክ በሶዶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የጤና ፕሮግራም ዘርፍ ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ በቀጣይ የልማት ፕሮግራሞች በይበልጥ ጥራቱ የተጠበቀ ከማድረግ ረገድ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ኤካ በበኩላቸው ባለፈው በጀት ዓመት በበሽታ መከላከል የእናቶችንና የሕፃናትን ሞት በመቀነስ ረገድ ጠንካራ ተግባራት የተከናወኑ ሲሆን በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።
ዘጋቢ: ፀሐይ ጎበና – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል