ፍትሀዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራትን ለማሳደግ በትኩረት መስራት ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 21/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትሀዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራትን ለማሳደግ በትኩረት መሰራት እንደሚገባ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ዓመታዊ የዕቅድ አፈፃፀምና ግምገማ መድረክ በሶዶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የጤና ፕሮግራም ዘርፍ ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ በቀጣይ የልማት ፕሮግራሞች በይበልጥ ጥራቱ የተጠበቀ ከማድረግ ረገድ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ኤካ በበኩላቸው ባለፈው በጀት ዓመት በበሽታ መከላከል የእናቶችንና የሕፃናትን ሞት በመቀነስ ረገድ ጠንካራ ተግባራት የተከናወኑ ሲሆን በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።
ዘጋቢ: ፀሐይ ጎበና – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ አጠቃላይ የትምህርት ጥራት፣ ቁጥጥርና የደረጃ ምዘና የአሰራር ስርዓት ለውጥ እየታየበት መምጣቱ ተገለጸ
በወሊድ ምክንያት የሚሞቱ እናቶችን ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
የፃማኮ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ የ”ባርባይሳ” በዓል የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫ፣ የሰላምና የመተሳሰብ ምልክትነቱን በማግዘፍ ለዓለም አደባባይ ማብቃት ይገባል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ገለጹ