የቅዱስ ገብርኤል በአለ ንግስ ያለምንም የፀጥታ ችግር በታላቅ ድምቀት ተከብሮ መዋሉን የጋሞ ዞን ፖሊስ ገለፀ
ህብረተሰቡም ላደረገው ቀና ትብብር የዞኑ ፖሊስ ምስጋና አቅርቧል።
የጋሞ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር አብረሀም ቡኤ፤ የመልዓኩ የቅዱስ ገብርኤል በአል በዞኑ ባሉ አድባራት ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ መዋሉን አስታውቀዋል።
አክለውም ህብረተሰቡ የትራፊክ አደጋም ሆነ የፀጥታ ችግር እንዳይፈጠር ላደረገው ቀና ትብብር ምስጋና አቅርበዋል።
በተመሳሳይ ታሪካዊው እና በፌደራል ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን የተመዘገበው የኤሊው ቅዱስ ገብርኤል በአለ ንግስ በሰላም ተከብሮ መዋሉን የዳራማሎ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ቡካ ቡላቻ አስታውቀዋል።
ገዳሙ ታሪካዊ በመሆኑ በአሉን ለማክበር ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን የተሳተፉ ሲሆን እንግዶችን በመቀበልና በመሸኘት ህብረተሰቡ ላደረገው ቀና ትብብር አመስግነዋል።
ዘጋቢ፡ ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
የቅዱስ ገብርኤል በአለ ንግስ ያለምንም የፀጥታ ችግር በታላቅ ድምቀት ተከብሮ መዋሉን የጋሞ ዞን ፖሊስ ገለፀ

More Stories
የቡርጂ ዞን ምክር ቤት አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ ሾመ
የወባ በሽታ ስርጭትን የመከላከልና የመቆጣጠርን ጉዳይ ቀዳሚ ተግባር አድርጎ እየሰራ መሆኑን የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ አስታወቀ
አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ተገልጋዩን ለማርካት እየሰራ መሆኑን የአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል አስታወቀ