የቅዱስ ገብርኤል በአለ ንግስ ያለምንም የፀጥታ ችግር በታላቅ ድምቀት ተከብሮ መዋሉን የጋሞ ዞን ፖሊስ ገለፀ
ህብረተሰቡም ላደረገው ቀና ትብብር የዞኑ ፖሊስ ምስጋና አቅርቧል።
የጋሞ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር አብረሀም ቡኤ፤ የመልዓኩ የቅዱስ ገብርኤል በአል በዞኑ ባሉ አድባራት ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ መዋሉን አስታውቀዋል።
አክለውም ህብረተሰቡ የትራፊክ አደጋም ሆነ የፀጥታ ችግር እንዳይፈጠር ላደረገው ቀና ትብብር ምስጋና አቅርበዋል።
በተመሳሳይ ታሪካዊው እና በፌደራል ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን የተመዘገበው የኤሊው ቅዱስ ገብርኤል በአለ ንግስ በሰላም ተከብሮ መዋሉን የዳራማሎ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ቡካ ቡላቻ አስታውቀዋል።
ገዳሙ ታሪካዊ በመሆኑ በአሉን ለማክበር ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን የተሳተፉ ሲሆን እንግዶችን በመቀበልና በመሸኘት ህብረተሰቡ ላደረገው ቀና ትብብር አመስግነዋል።
ዘጋቢ፡ ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
የቅዱስ ገብርኤል በአለ ንግስ ያለምንም የፀጥታ ችግር በታላቅ ድምቀት ተከብሮ መዋሉን የጋሞ ዞን ፖሊስ ገለፀ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል