የቅዱስ ገብርኤል በአለ ንግስ ያለምንም የፀጥታ ችግር በታላቅ ድምቀት ተከብሮ መዋሉን የጋሞ ዞን ፖሊስ ገለፀ

የቅዱስ ገብርኤል በአለ ንግስ ያለምንም የፀጥታ ችግር በታላቅ ድምቀት ተከብሮ መዋሉን የጋሞ ዞን ፖሊስ ገለፀ

‎ህብረተሰቡም ላደረገው ቀና ትብብር የዞኑ ፖሊስ ምስጋና አቅርቧል።

‎የጋሞ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር አብረሀም ቡኤ፤ የመልዓኩ የቅዱስ ገብርኤል በአል በዞኑ ባሉ አድባራት ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ መዋሉን አስታውቀዋል።

‎አክለውም ህብረተሰቡ የትራፊክ አደጋም ሆነ የፀጥታ ችግር እንዳይፈጠር ላደረገው ቀና ትብብር ምስጋና አቅርበዋል።

‎በተመሳሳይ ታሪካዊው እና በፌደራል ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን የተመዘገበው የኤሊው ቅዱስ ገብርኤል በአለ ንግስ በሰላም ተከብሮ መዋሉን የዳራማሎ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ቡካ ቡላቻ አስታውቀዋል።

‎ገዳሙ ታሪካዊ በመሆኑ በአሉን ለማክበር ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን የተሳተፉ ሲሆን እንግዶችን በመቀበልና በመሸኘት ህብረተሰቡ ላደረገው ቀና ትብብር አመስግነዋል።

‎ዘጋቢ፡ ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን