የባስኬቶ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ እያተካሄደ ነው

የባስኬቶ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ እያተካሄደ ነው

የባስኬቶ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ አስቴር ሰነቀ በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትና እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ እንዲሁም የ2018 በጀት ዓመት የምክር ቤቱ ተግባራት ማስፈፀሚያ በጀት ለምክር ቤት አባላት አቅርበዋል።

በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ የምክር ቤቱ አባላት ሀሳብ አስተያየቶችን በመስጠት በሙሉ ድምጽ አጽድቀዋል።

የዞኑ አስተዳደር ምክር የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ በኢንጂነር ፍሬዉ ፍሻለዉ በኩል እየቀረበ ይገኛል።

ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን