የወላይታ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13ኛ የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው
የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ጤናዬ ትርንጎ በመክፈቻ ንግግራቸው የዞኑ ህዝብ የሚያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በተገቢው ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤቶች ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ጠንካራ ሥራ ተሰርቶ የላቀ ውጤት መመዝገቡንም ጠቁመዋል።
ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለመከላከል ብርቱ ጥረት እየተደረገ ያለ ቢሆንም ውስንነት እንዳለ በማንሳት፤ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ከወረዳና ቀበሌ ምክር ቤቶች ጋር በመቀናጀት ሰፊ ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ጉባኤው በ8 አጀንዳዎች ላይ በመምከር ውሳኔ የሚያስተላልፍ ሲሆን በ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ በቀለች ጌቾ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል