የወላይታ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13ኛ የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው

የወላይታ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13ኛ የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው

የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ጤናዬ ትርንጎ በመክፈቻ ንግግራቸው የዞኑ ህዝብ የሚያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በተገቢው ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤቶች ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ጠንካራ ሥራ ተሰርቶ የላቀ ውጤት መመዝገቡንም ጠቁመዋል።

ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለመከላከል ብርቱ ጥረት እየተደረገ ያለ ቢሆንም ውስንነት እንዳለ በማንሳት፤ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ከወረዳና ቀበሌ ምክር ቤቶች ጋር በመቀናጀት ሰፊ ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

ጉባኤው በ8 አጀንዳዎች ላይ በመምከር ውሳኔ የሚያስተላልፍ ሲሆን በ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል።

ዘጋቢ፡ በቀለች ጌቾ – ከዋካ ጣቢያችን