የወላይታ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13ኛ የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው
የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ጤናዬ ትርንጎ በመክፈቻ ንግግራቸው የዞኑ ህዝብ የሚያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በተገቢው ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤቶች ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ጠንካራ ሥራ ተሰርቶ የላቀ ውጤት መመዝገቡንም ጠቁመዋል።
ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለመከላከል ብርቱ ጥረት እየተደረገ ያለ ቢሆንም ውስንነት እንዳለ በማንሳት፤ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ከወረዳና ቀበሌ ምክር ቤቶች ጋር በመቀናጀት ሰፊ ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ጉባኤው በ8 አጀንዳዎች ላይ በመምከር ውሳኔ የሚያስተላልፍ ሲሆን በ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ በቀለች ጌቾ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ