በክልሉ በሚገኙ የግል ድርጅቶች ላይ ተቀጥረው የሚሰሩ ስራተኞች መብታቸውና ጥቅማቸው ተከብሮ መስራት እንዲችሉ በማህበር መደራጀት እንደሚያፈልግ ተገለጸ
በክልሉ በሚገኙ የግል ድርጅቶች ላይ ተቀጥረው የሚሰሩ ስራተኞች መብታቸውና ጥቅማቸው ተከብሮና ተጠብቆ መስራት እንዲችሉ በማህበር መደራጀት እንደሚያፈልግ በኢትዮጵያ ሠራተኞች ማሕበራት ኮንፌደሬሽን የደቡብ ምዕራብ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
ጽ/ቤቱ በ2018 በጀት ዓመት በክልሉ የሚገኙ ነባር ማህበራትን አቅም ለመገንባትና አዳዲስ ማሕበራትን ለማቋቋም ቀዳሚ ተግባሩ አድርጎ እንደሚሰራም ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማህበራት ኮንፌደሬሽን በመላ ሀገሪቱ የነበሩትን ቅርንጫፎች ለማሳደግ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሚዛን አማን ከተማ ከመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ጀምሮ ጽ/ቤት በመክፈት እየሰራ እንደሚገኝ የጽ/ቤቱ ሀላፊ አቶ ኢሳያስ አይሳ ገልጸዋል።
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ወደ ስራ ከገባ ወዲህ በክልሉ በሙሌጌ መሠረታዊ ሠራተኞች ማህበርና በሙሌጌ አግሮ ኢንዱስትሪ መካከል የተፈጠረውን የህብረት ስምምነት ክርክር ለሁለት ዓመታት ቆይቶ የነበረውን በማስተካከል ወደ መስማማት እንዲመጡ መደረጉን ለአብነት አንስተዋል።
በክልሉ በሚገኙ ስድስት ዞኖች 28 የተደራጁ ማህበራት እንዳሉ አቶ ኢሳያስ አንስተው፤ ጽ/ቤቱ በክልሉ ስራ ከጀመረ ወዲህም 200 አባል የያዘውን አንድ ማህበር ማደራጀታቸውን አብራርተዋል።
በክልሉ በርካታ የኢንቨስትመንት አማራጮች በመኖራቸው ምክንያት በርካታ የግል ድርጅቶች ቢኖሩም በማህበር የተደራጁት ጥቂቶች መሆናቸውን አቶ ኢሳያስ ጠቁመው፤ በ2018 በጀት ነባር ማህበራትን አቅም ማጎልበት ያልተደራጁትን የማደራጀት ስራ ከባለድርሻ አካላት ጋር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ ወሰኑ ወዳጆ – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ አጠቃላይ የትምህርት ጥራት፣ ቁጥጥርና የደረጃ ምዘና የአሰራር ስርዓት ለውጥ እየታየበት መምጣቱ ተገለጸ
በወሊድ ምክንያት የሚሞቱ እናቶችን ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
የፃማኮ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ የ”ባርባይሳ” በዓል የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫ፣ የሰላምና የመተሳሰብ ምልክትነቱን በማግዘፍ ለዓለም አደባባይ ማብቃት ይገባል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ገለጹ