የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሔድ ጀመረ
ሀዋሳ: ሐምሌ 16/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ በተለዩ ዘጠኝ አጀንዳዎች ዙሪያ በጥልቀት እንደሚመክር ተመላክቷል።
ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚካሔደው የምክር ቤቱ 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባዔ፥ ከምክር ቤት አባላት በተጨማሪ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሕዝብ ክንፍ አደረጃጀቶች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
በጉባኤውም የ2017 በጀት ዓመት የአስፈፃሚ አካላት፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2018 አስፈፃሚ አካላት መሪ እቅድ፣ እና ሌሎች ተያያዥ አጀንዳዎች ቀርበው ጥልቅ ውይይት ይደረግባቸዋል።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ
More Stories
በተጠናቀቀው በጀት አመት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ገለጹ
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን ልዩ አርማ ሆኖ በታሪክ አሻራ ይመዘገባል ሲሉ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ገለፁ
ወጣቶች የነገ ለምለምና ውብ ሀገርን ለመረከብ ከአካባቢ ጀምሮ በበጎ ተግባራት በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው ተጠቆመ