የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሔድ ጀመረ
ሀዋሳ: ሐምሌ 16/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ በተለዩ ዘጠኝ አጀንዳዎች ዙሪያ በጥልቀት እንደሚመክር ተመላክቷል።
ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚካሔደው የምክር ቤቱ 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባዔ፥ ከምክር ቤት አባላት በተጨማሪ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሕዝብ ክንፍ አደረጃጀቶች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
በጉባኤውም የ2017 በጀት ዓመት የአስፈፃሚ አካላት፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2018 አስፈፃሚ አካላት መሪ እቅድ፣ እና ሌሎች ተያያዥ አጀንዳዎች ቀርበው ጥልቅ ውይይት ይደረግባቸዋል።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
በክልሉ አጠቃላይ የትምህርት ጥራት፣ ቁጥጥርና የደረጃ ምዘና የአሰራር ስርዓት ለውጥ እየታየበት መምጣቱ ተገለጸ
በወሊድ ምክንያት የሚሞቱ እናቶችን ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
የፃማኮ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ የ”ባርባይሳ” በዓል የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫ፣ የሰላምና የመተሳሰብ ምልክትነቱን በማግዘፍ ለዓለም አደባባይ ማብቃት ይገባል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ገለጹ