የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሔድ ጀመረ
ሀዋሳ: ሐምሌ 16/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ በተለዩ ዘጠኝ አጀንዳዎች ዙሪያ በጥልቀት እንደሚመክር ተመላክቷል።
ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚካሔደው የምክር ቤቱ 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባዔ፥ ከምክር ቤት አባላት በተጨማሪ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሕዝብ ክንፍ አደረጃጀቶች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
በጉባኤውም የ2017 በጀት ዓመት የአስፈፃሚ አካላት፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2018 አስፈፃሚ አካላት መሪ እቅድ፣ እና ሌሎች ተያያዥ አጀንዳዎች ቀርበው ጥልቅ ውይይት ይደረግባቸዋል።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ