የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ጉባኤ ተጠናቀቀ
ባለፉት ሁለት ቀናት በታርጫ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ተጠናቅቋል።
በርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አቅራቢነት የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ሆነው የቀረቡ ዶክተር አብይ አንደሞን የምክር ቤት አባላት በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
የስራና ክህሎት ቢሮ ሆነው የተሾሙት ዶክተር አብይ አንደሞ በምክር ቤቱ ፊት ቆመው ቃለ መሃለ ፈጽመዋል።
ምክር ቤቱ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት የቀረበውን የዳኞች ከዳኝነት ስንብት የቀረቡለትን ዝርዝር ሀሳብ የምክር ቤት አባላት በመምከር ውሳኔውን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ

More Stories
በክልሉ አጠቃላይ የትምህርት ጥራት፣ ቁጥጥርና የደረጃ ምዘና የአሰራር ስርዓት ለውጥ እየታየበት መምጣቱ ተገለጸ
በወሊድ ምክንያት የሚሞቱ እናቶችን ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
የፃማኮ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ የ”ባርባይሳ” በዓል የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫ፣ የሰላምና የመተሳሰብ ምልክትነቱን በማግዘፍ ለዓለም አደባባይ ማብቃት ይገባል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ገለጹ