የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ጉባኤ ተጠናቀቀ
ባለፉት ሁለት ቀናት በታርጫ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ተጠናቅቋል።
በርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አቅራቢነት የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ሆነው የቀረቡ ዶክተር አብይ አንደሞን የምክር ቤት አባላት በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
የስራና ክህሎት ቢሮ ሆነው የተሾሙት ዶክተር አብይ አንደሞ በምክር ቤቱ ፊት ቆመው ቃለ መሃለ ፈጽመዋል።
ምክር ቤቱ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት የቀረበውን የዳኞች ከዳኝነት ስንብት የቀረቡለትን ዝርዝር ሀሳብ የምክር ቤት አባላት በመምከር ውሳኔውን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል