የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ጉባኤ ተጠናቀቀ
ባለፉት ሁለት ቀናት በታርጫ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ተጠናቅቋል።
በርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አቅራቢነት የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ሆነው የቀረቡ ዶክተር አብይ አንደሞን የምክር ቤት አባላት በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
የስራና ክህሎት ቢሮ ሆነው የተሾሙት ዶክተር አብይ አንደሞ በምክር ቤቱ ፊት ቆመው ቃለ መሃለ ፈጽመዋል።
ምክር ቤቱ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት የቀረበውን የዳኞች ከዳኝነት ስንብት የቀረቡለትን ዝርዝር ሀሳብ የምክር ቤት አባላት በመምከር ውሳኔውን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ

More Stories
በክልሉ ባለፉ 6 ወራት ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ
ዘመናዊ የግብርና ግብአት እና ቴክኖሎጂን በተገቢው በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ የቀቤና ልዩ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለፀ