የህብረ ብሔራዊነት ማሳያ የሆነው የህዳሴው ግድብ ዋንጫ በራስ አቅም የመቻላችን ምልክት ነው ሲሉ የደቡብ ኦሞ ዞን አርብቶ አደሮች ተናገሩ
ይህን የተናገሩት የህዳሴው ግድብ ዋንጫ በዞኑ ማዕከል ዲመካ ከተማ በገባበት ወቅት ነው።
አስተያየታቸውን የሰጡን አንዳንድ አርብቶ አደሮች እንደገለፁት፤ የህዳሴው ግድብ ዋንጫ የህብረ ብሔራዊነት ማሳያ ምልክት ከመሆኑም በላይ በመተባበር እና በአንድነት ከተሰራ የማይረጋገጥ ልማት እንደሌለ ያየንበት ነው።
አክለውም ኢትዮጵያ ያለመቻል ትርክቶቿን የሰበረች በመተባበር በአንድነት ጀምሮ መጨረስን ያረጋገጠችበት የሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች አሻራ ያረፈበት ግድብ በመሆኑ ኩራት እንደሚሰማቸው ገልፀዋል።
ብድርና ዕርዳታ በመከልከል ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የማይነጥፍ ሀብት አውጥታ እንዳትጠቀም ለማድረግ አሉባልታ ቢረጭም ኢትዮጵያ አሁንም በጋራ ተጠቃሚነት መርህ በራሷ አቅም ገንብታ ለማስመረቅ በቅታለች ሲሉ ገልፀዋል።
አሁንም ቀሪ ሥራው ተጠናቆ ሪቫን እስኪቆረጥ ድረስ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ በማድረግ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልፀው፤ በቀጣይም እንደ ህዳሴው ግድብ በሌሎች የልማት ዘርፎች የሚያደርጉትን ድጋፍና አንድነት እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ