የህብረ ብሔራዊነት ማሳያ የሆነው የህዳሴው ግድብ ዋንጫ በራስ አቅም የመቻላችን ምልክት ነው ሲሉ የደቡብ ኦሞ ዞን አርብቶ አደሮች ተናገሩ
ይህን የተናገሩት የህዳሴው ግድብ ዋንጫ በዞኑ ማዕከል ዲመካ ከተማ በገባበት ወቅት ነው።
አስተያየታቸውን የሰጡን አንዳንድ አርብቶ አደሮች እንደገለፁት፤ የህዳሴው ግድብ ዋንጫ የህብረ ብሔራዊነት ማሳያ ምልክት ከመሆኑም በላይ በመተባበር እና በአንድነት ከተሰራ የማይረጋገጥ ልማት እንደሌለ ያየንበት ነው።
አክለውም ኢትዮጵያ ያለመቻል ትርክቶቿን የሰበረች በመተባበር በአንድነት ጀምሮ መጨረስን ያረጋገጠችበት የሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች አሻራ ያረፈበት ግድብ በመሆኑ ኩራት እንደሚሰማቸው ገልፀዋል።
ብድርና ዕርዳታ በመከልከል ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የማይነጥፍ ሀብት አውጥታ እንዳትጠቀም ለማድረግ አሉባልታ ቢረጭም ኢትዮጵያ አሁንም በጋራ ተጠቃሚነት መርህ በራሷ አቅም ገንብታ ለማስመረቅ በቅታለች ሲሉ ገልፀዋል።
አሁንም ቀሪ ሥራው ተጠናቆ ሪቫን እስኪቆረጥ ድረስ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ በማድረግ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልፀው፤ በቀጣይም እንደ ህዳሴው ግድብ በሌሎች የልማት ዘርፎች የሚያደርጉትን ድጋፍና አንድነት እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል