የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ማካሄድ ጀመረ
የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወንድሙ ኩርታ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ ምክር ቤቱ በህገመንግስት የተሰጠውን ስልጣን በመጠቀም የአስፈፃሚ አካላትን አፈፃፀም ገምግሞ ግብረመልስ ሰጥቷል ብለዋል።
በግብርና ስራ የመጣውን ለውጥ ማስቀጠል እንደሚገባ ያነሱት አፈ ጉባዔው በትምህርት ረገድ የትምህርት ለሁሉም ንቅናቄን ማስፋት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
በጉባኤው የ2017 በጀት አመት የአስፈጻሚ አካላት የስራ አፈፃፀም ሪፖርትና ቀጣይ ዕቅድ ውይይት ይደረግበታል፡፡
በሚቀርቡ አጀንዳዎች ላይ በምክር ቤቱ አባላት ጥያቄና አስተያየት ተነስቶ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እና በካቢኒያቸው ምላሽ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የምክር ቤቱ ጉባዔ በደቡብ ቴሌቪዥን፣ በድርጅቱ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ፌስቡክና ዩቲዩብ በቀጥታ ይሰራጫል፡፡
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ማካሄድ ጀመረ

More Stories
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ