የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ማካሄድ ጀመረ
የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወንድሙ ኩርታ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ ምክር ቤቱ በህገመንግስት የተሰጠውን ስልጣን በመጠቀም የአስፈፃሚ አካላትን አፈፃፀም ገምግሞ ግብረመልስ ሰጥቷል ብለዋል።
በግብርና ስራ የመጣውን ለውጥ ማስቀጠል እንደሚገባ ያነሱት አፈ ጉባዔው በትምህርት ረገድ የትምህርት ለሁሉም ንቅናቄን ማስፋት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
በጉባኤው የ2017 በጀት አመት የአስፈጻሚ አካላት የስራ አፈፃፀም ሪፖርትና ቀጣይ ዕቅድ ውይይት ይደረግበታል፡፡
በሚቀርቡ አጀንዳዎች ላይ በምክር ቤቱ አባላት ጥያቄና አስተያየት ተነስቶ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እና በካቢኒያቸው ምላሽ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የምክር ቤቱ ጉባዔ በደቡብ ቴሌቪዥን፣ በድርጅቱ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ፌስቡክና ዩቲዩብ በቀጥታ ይሰራጫል፡፡
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ማካሄድ ጀመረ

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ