የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ማካሄድ ጀመረ
የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወንድሙ ኩርታ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ ምክር ቤቱ በህገመንግስት የተሰጠውን ስልጣን በመጠቀም የአስፈፃሚ አካላትን አፈፃፀም ገምግሞ ግብረመልስ ሰጥቷል ብለዋል።
በግብርና ስራ የመጣውን ለውጥ ማስቀጠል እንደሚገባ ያነሱት አፈ ጉባዔው በትምህርት ረገድ የትምህርት ለሁሉም ንቅናቄን ማስፋት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
በጉባኤው የ2017 በጀት አመት የአስፈጻሚ አካላት የስራ አፈፃፀም ሪፖርትና ቀጣይ ዕቅድ ውይይት ይደረግበታል፡፡
በሚቀርቡ አጀንዳዎች ላይ በምክር ቤቱ አባላት ጥያቄና አስተያየት ተነስቶ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እና በካቢኒያቸው ምላሽ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የምክር ቤቱ ጉባዔ በደቡብ ቴሌቪዥን፣ በድርጅቱ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ፌስቡክና ዩቲዩብ በቀጥታ ይሰራጫል፡፡
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ማካሄድ ጀመረ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል