የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤ ሁለተኛ ቀን ውሎ እየተካሔደ ነው
ሀዋሳ: ሐምሌ 12/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤ ሁለተኛ ቀን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የአስፈፃሚ መ/ቤቶችን የ2017 በጀት አመት አፈጻጸም ባቀረቡት ሪፖርት መነሻ ያደረገ ጥያቄና አስተያየት በምክር ቤት አባላት እየቀረበ ነው።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤ የአስፈፃሚ መ/ቤቶችን የ2017 በጀት አመት አፈጻጸም ሪፖርት መነሻ በማድረግ የምክር ቤቱ አባላት ምላሽና ማብራሪያ በሚሹ ጉዳዮች ዙሪያ ሃሳብ እና አስተያየት በማቅረብ ላይ ናቸው።
ምክር ቤቱ በዛሬው መርሃ ግብር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሚሰጡ ይሆናል።
በጉባኤው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት አስፈፃሚ አካላት፣ አፈ-ጉባኤዎች፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶች፣ የሪጂዮ ፖሊስ ከተሞች አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በመሳተፍ ላይ ናቸዉ።
ዘጋቢ፡ ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል