በበጀት ዓመቱ ልዩ ትኩረት የተሰጣቸው ጉዳዮች ላይ በማተኮር መሰራቱን በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የቦንጋ ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
ቅርንጫፍ ጣቢያው በ2017 በጀት ዓመት የተከናወኑ ተግባራትን ገምግሟል።
የቅርንጫፍ ጣቢያው ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ስንታየሁ ሳልልህ፤ በበጀት ዓመቱ ልዩ ትኩረት በተሰጣቸው ጉዳዮች ላይ በማተኮር ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል፡፡
በሁሉም ዘርፎች በክልላዊና ሀገራዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን አንስትዋል።
ወጣቶች በሀገረ-መንግስት ግንባታ ያላቸውን ሚና፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን፣ የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማት እንቅስቃሴዎችን፣ የአረንጓዴ አሻራን፣ የሌማት ትሩፋትንና ሌሎችንም በርካታ ጉዳዮችን በተመለከተ መረጃዎችን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን አቶ ስንታየሁ አንስተዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በ2017 በጀት ዓመት የተከናወኑ ተግባራት የተሻሉ መሆናቸውን በመግለጽ፤ በቀጣይ መስተካከል ያሉባቸውን ጉዳዮችም ጠቁመዋል፡፡
ህብረተሰቡን ያሳተፉ ወቅታዊና ሚዛናዊ የሆኑ ዘገባዎችን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በቀጣይ መስራት እንደሚገባ ተገልጿል፡፡
ዘጋቢ፡ ትዕግስቱ ጴጥሮስ – ከቦንጋ ጣቢያችን
More Stories
ወጣቶች የክረምት ጊዜያቸውን ህዝብን ሊጠቅሙ በሚችሉ በጎ ተግባራት ላይ በመሳተፍ ማሳለፍ እንደሚገባ ተገለጸ
የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎችን በማስፋፋት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን የቦንጋ ዩኒቨርስቲ ገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ በኣሪ ዞን በደቡብ ኣሪ ወረዳ በኮመር ቀበሌ በመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች ከ6 መቶ ሺህ ብር በላይ ግምት ያላቸውን የዕለት ደራሽ ቁሳቁሶች ድጋፍ አደረገ