በበጀት ዓመቱ ልዩ ትኩረት የተሰጣቸው ጉዳዮች ላይ በማተኮር መሰራቱን በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የቦንጋ ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
ቅርንጫፍ ጣቢያው በ2017 በጀት ዓመት የተከናወኑ ተግባራትን ገምግሟል።
የቅርንጫፍ ጣቢያው ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ስንታየሁ ሳልልህ፤ በበጀት ዓመቱ ልዩ ትኩረት በተሰጣቸው ጉዳዮች ላይ በማተኮር ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል፡፡
በሁሉም ዘርፎች በክልላዊና ሀገራዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን አንስትዋል።
ወጣቶች በሀገረ-መንግስት ግንባታ ያላቸውን ሚና፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን፣ የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማት እንቅስቃሴዎችን፣ የአረንጓዴ አሻራን፣ የሌማት ትሩፋትንና ሌሎችንም በርካታ ጉዳዮችን በተመለከተ መረጃዎችን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን አቶ ስንታየሁ አንስተዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በ2017 በጀት ዓመት የተከናወኑ ተግባራት የተሻሉ መሆናቸውን በመግለጽ፤ በቀጣይ መስተካከል ያሉባቸውን ጉዳዮችም ጠቁመዋል፡፡
ህብረተሰቡን ያሳተፉ ወቅታዊና ሚዛናዊ የሆኑ ዘገባዎችን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በቀጣይ መስራት እንደሚገባ ተገልጿል፡፡
ዘጋቢ፡ ትዕግስቱ ጴጥሮስ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል