በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የአርባምንጭ ቅርንጫፍ ጣቢያ ወቅታዊ እና ተአማኒ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ከማድረግ አኳያ በትጋት እየሰራ መሆኑ ተገለጸ

በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የአርባምንጭ ቅርንጫፍ ጣቢያ ወቅታዊ እና ተአማኒ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ከማድረግ አኳያ በትጋት እየሰራ መሆኑ ተገለጸ

የአርባምንጭ ቅርንጫፍ ጣቢያ ጽህፈት ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምና የ2018 ጠቋሚ ዕቅድ ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሂዷል።

ጣቢያው በጋሞ፣ ኮንሶ እና ጋርዱላ ዞኖች የሚገኙ 8 ብሄረሰብ ቋንቋዎች አማርኛን ጨምሮ በ9 ቋንቋዎች ማህበረሰቡን እያገለገለ ይገኛል።

በተካሄደው የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሪፖርትና የ2018 ዕቅድ ግምገማ ላይ የጣቢያው ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጉጃ ጉሜ፤ ተቋሙ በሚዲያ ቴክኖሎጂ፣ በሬዲዮና ቴሌቪዥን ዜናና ፕሮግራም፣ በንጋት ጋዜጣ ስርጭት፣ በማስታወቂያ እና በሌሎችም ዘርፎች የተሻለ ውጤት ማስመዝገቡን አብራርተዋል።

ዋና ስራ አስኪያጁ ተቋሙን በቴክኖሎጂ እቃዎች ለማደራጀት እና ይበልጥ ተደራሽ እንዲሆን የሚመለከታቸው አካላት እንዲደግፉ ጠይቀዋል።

2018 በጀት ዓመት በቀረበው ጠቋሚ ዕቅድ በ8 ብሄረሰብ ቋንቋዎች እንዲሁም በደቡብ ሬዲዮ፣ ቴሌቪዥን፣ በማህበራዊ ሚዲያ የተለያዩ አማራጮች ወቅታዊና አዝናኝ ዜና እና ፕሮግራሞችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱን አስረድተዋል።

የተቋሙ ሠራተኞች ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር እና ወቅታዊ መረጃዎችን ተደራሽ ከማድረግ አኳያ የተጀመረውን ሥራ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

በውይይቱ ላይ የተቋሙ ዋና ስራ አስኪያጅ፣ የጣቢያው ምክትል ስራ አስኪያጅና የይዘት ዘርፍ አስተባባሪ አቶ በሀይሉ ሙሉጌታ፣ የዘርፍ አስተባባሪዎች፣ አርታኢዎች፣ ተርጓሚዎች እና ሌሎች የተቋሙ ሰራተኞች ተገኝተዋል።

ዘጋቢ: አማሮ አርሳባ – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን