የምስራቅ ጉራጌ ዞን አስተዳደር ከዞኑ ከተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በቡታጅራ ከተማ ወይይት በማካሄድ ላይ ይገኛል
በዞኑ በልማት፣ በሰላምና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ በተሰሩ ስራዎች ላይ ያተኮረ ውይይት የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን፣ የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሰለ ጫካ በተገኙበት ከዞኑ ከተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በቡታጅራ ከተማ ውይይት በመካሄድ ላይ ነው።
ከዞኑ ምስረታ በኋላ የልማት፣ የሰላምና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን መሠረት ያደረገ ንግግር ያደረጉት የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳደሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን፤ በዞኑ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የህዝቡን አብሮነት መሠረት ያደረጉ ሰራዎች በመሠራታቸው ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል፡፡
ለዚህ ውጤት መመዝገብ የሀገር ሽማግሌዎና የሀይማኖት አባቶች ወጣቶችን ለሰላም በማሰለፍ ያደረጉት አስተዋፅኦ የማይተካ መሆኑን አመላክተዋል።
በኦሮሚያ አጎራባች ወረዳዎች አመራሮች ጋር ቅንጅታዊ ስራ በመሠራቱ የህዝብ ለህዝብ ትስስሩ መጠናከሩን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን ተናግረዋል።
በግብርና፣ በስራ ዕድል ፈጠራ፣ በኢንቨስትመንት፣ በገቢ አሰባሰብ እና የሰንበት ገበያ በማስፋፋት የኑሮ ውድነትን ለማርገብ የተሰሩ ስራዎችን በዝርዝር አንስተዋል።
በክልሉ ተሞክሮ ሊሆን የሚችል የኮሪደር ልማት ስራዎች መኖራቸውን የዞኑ አስተዳደር የተናገሩ ሲሆን መድረኩ ከዞኑ ህዝብ ጋራ መግባባት ለመፍጠር የሚረዳ መሆኑን አንስተዋል።
በዞኑ የተሰሩ ስራዎች ሰነድ በመቅረብ ላይ የሚገኙ ሲሆን በቀረበው ሰነድ ላይ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ፋሲል ሀይሉ

More Stories
የቡርጂ ዞን ምክር ቤት አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ ሾመ
የወባ በሽታ ስርጭትን የመከላከልና የመቆጣጠርን ጉዳይ ቀዳሚ ተግባር አድርጎ እየሰራ መሆኑን የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ አስታወቀ
አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ተገልጋዩን ለማርካት እየሰራ መሆኑን የአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል አስታወቀ