በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን ምስራቅ መስቃን ወረዳ ወጀባቴ ቀበሌ ንቡር ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፈት ሆነ
ጤና ኬላው በመንግስትና ህብረተሰብ ተሳትፎ የተገነባ ሲሆን በአጠቃላይ 13 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ፈጅቷል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአንድ ወረዳ ኢኒሼቲቭ ማዕከል የሆነው ይህ ሁሉ አቀፍ ጤና ተቋም፤ የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊ፣ የዞኑ እና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በድምቀት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ፤ በእለቱ የተመረቀው ንቡር ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ በክልሉ በተጠናቀቀዉ በጀት አመት ከተገነቡት 17 ጤና ኬላዎች አንዱ ነው ብለዋል።
የህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ የሆነው ይህ ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ በጥራት የተሰራ መሆኑን አንስተው ሙሉ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ነው ብለዋል።
በአምስት ወራት ግንባታዉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ የአካባቢው ነዋሪዎች በገንዘብ እና በጉልበት ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን ከዚህ ቀደም በአካባቢው የህክምና ማዕከል ባለመኖሩ እናቶች በወሊድ ምክንያት ይሞቱ እደነበር ያነጋገርናቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ተናግረዋል።
የያነጋገርናቸዉ እናቶች ይህ ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ ከዚህ ቀደም ይገጥማቸዉ የነበረዉን እንግልት ሊቀርፍላቸዉ እደሚችል ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ አልማዝ ቢረዳ

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ