“በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዞናዊ ንቅናቄ መድረክ በመካሄድ ላይ ነው
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 04/2017 ዓ.ም (ደረቴድ) በወላይታ ዞን “በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዞናዊ ንቅናቄ መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ወጣቶች በበጎ አገልግሎት ላይ በስፋት እንዲሳተፉ በማድረግ የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ሌሎች ችግሮች በመፍታት የበጎ ፈቃደኝነት ባህል ለማጎልበት ዓላማ ያደረገ መሆኑ ተመላክቷል።
በዞኑ ዘንድሮ የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ ከ912 በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱ ተገልጿል።
በዚህም ከ572 ሺህ በላይ ወጣቶች እንደሚሳተፉ እና ከ550 ሚሊዮን 851 ሺህ በላይ የሚገመት ሀብት በወጣቶች ጉልበት ለማዳን ግብ ተጥሎ ይሰራል።
በመርሃግብሩ ላይ የተገኙት የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር አማረ አቦታ፥ የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ም/ኃላፊና የወጣት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ማርቆስ ማቴዎስ፣ የዞኑ የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ መስፍን ቶማስን ጨምሮ የዞን ማዕከል አጠቃላይ አመራሮች፣ የበጎ ፈቃድ ወጣቶችን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ናቸው።
ዘጋቢ፡ በቀለች ጌቾ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ