ከተሞችን ለነዋሪዎች ጽዱ፣ ውብና ምቹ ለማድርግ በቆሻሻ አወጋገድና አያያዝ ሥርዓት ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተማና መሠረት ልማት ቢሮ አሳሰበ
ቢሮው የክልሉ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ኢንሰቲትዩት ተቋም ጋር በጋራ በቆሻሻ አወጋገድ ጥናት ዙሪያ ምክክር መድረክ አካሂዷል።
በክልሉ ባሉ በ 6 ከተሞች የቆሻሻ አወጋገድና አያያዝ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ ጉድለት መኖሩ በጥናቱ ተረጋግጧል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ዘውዴ በከተሞች ውስጥ በተለያየ መልክ የሚመመነጩ አደገኛ ቆሻሻዎች መኖራቸውን ጠቅሰው በጥንቃቄና በአግባቡ ካልተወገዱ በከተሞች ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንደሚያደርሱ ገልፀዋል።
ቆሻሻ በአግባቡ ባለመወገዱ ለአካባቢ ብክለትና፣ ጎርፍ እና የተለያዩ በሽታዎች አየተከሰቱ በመሆናቸው ከተሞችን ለነዋሪዎች ፅድና ምቹ ለማድረግ ሁሉም በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ጥናት ምርምር የኢኮኖሚ ዘርፍ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ታምራት አሰፋ በበኩላቸው ቆሻሻ ከማመንጨት ጀምሮ አወጋገድ ሥርዓት ላይ ያተኮረ ጥናት በክልሉ 6 ከተሞች መካሄዱን ገልጸዋል።
በተለይም ከከተሞች መስፋፋትና የህዝብ ቁጥር መጨመር ጋር ተያይዞ የሚፈጠረው የቆሻሻ መጠን መጨመር በአከባቢ ላይ ከፍተኛ ጫና እየፈጠረ በመሆኑ ችግሩን ለመቅረፍ በህግ አግባብ ለመምራት የሚያስችል ጥናት ነው ብለዋል።
በመድረኩ በቆሻሻ አወጋገድና አያያዝ ዙሪያ ጥናት ቀርቦ ሰፊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን መድረኩ በጥናቱ ማሻሻያ ላይ ሀሳብ ተነስቶ ምላሸ ተሰጥቶበታል።
ዘጋቢ፡ አለሚቱ አረጋ

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ