ለምግብ እጥረት የተጋለጡ ነፍሰጡርና ለሚያጠቡ እናቶች እንድሁም ለህፃናት የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 01/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ ነፍሰጡርና ለሚያጠቡ እናቶች እንዲሁም ለህፃናት የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠሉን በዳውሮ ዞን የሎማ ቦሳ ወረዳ ሴቶች፣ ህፃናት፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡
የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ እታገኝ ኢሳያስ እንደገለፁት በሰቆጣ ቃልኪዳን የሚከናወኑ ተግባራት በወረዳው መቀንጨርን ዜሮ ለማድረስ የምግብና ሥርዓተ ምግብ ተግባራትን ሽፋን ከፍ በማድረግ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።
ድጋፍ በወረዳው ከሚገኙ ቀበሌያት መካከል ከፉላሣ ቦርዜ፣ ላላ አምቤ፣ ዚማ ዋሩማ፣ ጭጮ ሃዮ እና ከቱለማ ጣማ ቀበሌያት ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ ነፍሰጡርና ለሚያጠቡ እናቶች እንድሁም ለህፃናት ድጋፍ መደረጉን ወ/ሮ እታገኝ ተናግረዋ።
በሰቆጣ ቃል ኪዳን እስካሁን በተሰሩ ስራዎች በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡ መሆኑን የገለፁት ወ/ሮ እታገኝ፥ እናቶች በምግብ ራስን ከመቻል ባሻገር የአኗኗር ዘይቤ መቀየር የሚያስችሉ እንዲሁም ሌሎች ከዚህ ጋር የተያያዙ የግንዛቤ ሥራዎች መሰራቱን ገልጸዋል።
የወረዳው የህፃናት መብትና ደህንነት ማስጠበቅ ሥራ ሂደት አስተባባሪ ወ/ሮ ክብረዓለም በቀለ በበኩላቸው፥ የጨቅላ ህፃናት መቀንጨር ለመከላከልና በዚህም ሳቢያ ሊመጣ የሚችለውን ሞት ለመቀነስ የወተት ላም፣ በግና ፍየል እንዲሁም ዶሮ ግዢ በመፈጸም ስርጭት ማድረጉን አብራርተዋል።
በተጠናቀቀው በ2017 በጀት ዓመት በሰቆጣ ቃል ኪዳን ከ52 በላይ ህጻናትን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንና ከ50 በላይ ነፍሰጡርና የሚያጠቡ እናቶች በመርሃ ግብሩ ተጠቃሚ መሆናቸውን አመላክተዋል።
በፕሮግራሙ ከዚህ ቀደም የነበረውን የተመጣጠነ ምግብ እጥረት በተቻለ መልኩ ለማግኘት ጅምር የሚሆኑና የተሻለ ስራዎችም ተሰርተዋል ነው ያሉት።
ድጋፍ ካገኙ ነፍሰጡርና ከሚያጠቡ እናቶች መካከል አንዳንዶቹ በሰጡት አስተያየት “አሁን ያገኘሁት ድጋፍ የቆየውን የምግብ እጥረት ችግሩን የሚቀርፍ መሆኑን ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ አሸናፊ ግዛው – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
ህዝቡ የሚያነሳቸውን የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ ከመመለስ አኳያ የፍትህ ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አሳሰቡ
ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ