ለምግብ እጥረት የተጋለጡ ነፍሰጡርና ለሚያጠቡ እናቶች እንድሁም ለህፃናት የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 01/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ ነፍሰጡርና ለሚያጠቡ እናቶች እንዲሁም ለህፃናት የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠሉን በዳውሮ ዞን የሎማ ቦሳ ወረዳ ሴቶች፣ ህፃናት፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡
የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ እታገኝ ኢሳያስ እንደገለፁት በሰቆጣ ቃልኪዳን የሚከናወኑ ተግባራት በወረዳው መቀንጨርን ዜሮ ለማድረስ የምግብና ሥርዓተ ምግብ ተግባራትን ሽፋን ከፍ በማድረግ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።
ድጋፍ በወረዳው ከሚገኙ ቀበሌያት መካከል ከፉላሣ ቦርዜ፣ ላላ አምቤ፣ ዚማ ዋሩማ፣ ጭጮ ሃዮ እና ከቱለማ ጣማ ቀበሌያት ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ ነፍሰጡርና ለሚያጠቡ እናቶች እንድሁም ለህፃናት ድጋፍ መደረጉን ወ/ሮ እታገኝ ተናግረዋ።
በሰቆጣ ቃል ኪዳን እስካሁን በተሰሩ ስራዎች በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡ መሆኑን የገለፁት ወ/ሮ እታገኝ፥ እናቶች በምግብ ራስን ከመቻል ባሻገር የአኗኗር ዘይቤ መቀየር የሚያስችሉ እንዲሁም ሌሎች ከዚህ ጋር የተያያዙ የግንዛቤ ሥራዎች መሰራቱን ገልጸዋል።
የወረዳው የህፃናት መብትና ደህንነት ማስጠበቅ ሥራ ሂደት አስተባባሪ ወ/ሮ ክብረዓለም በቀለ በበኩላቸው፥ የጨቅላ ህፃናት መቀንጨር ለመከላከልና በዚህም ሳቢያ ሊመጣ የሚችለውን ሞት ለመቀነስ የወተት ላም፣ በግና ፍየል እንዲሁም ዶሮ ግዢ በመፈጸም ስርጭት ማድረጉን አብራርተዋል።
በተጠናቀቀው በ2017 በጀት ዓመት በሰቆጣ ቃል ኪዳን ከ52 በላይ ህጻናትን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንና ከ50 በላይ ነፍሰጡርና የሚያጠቡ እናቶች በመርሃ ግብሩ ተጠቃሚ መሆናቸውን አመላክተዋል።
በፕሮግራሙ ከዚህ ቀደም የነበረውን የተመጣጠነ ምግብ እጥረት በተቻለ መልኩ ለማግኘት ጅምር የሚሆኑና የተሻለ ስራዎችም ተሰርተዋል ነው ያሉት።
ድጋፍ ካገኙ ነፍሰጡርና ከሚያጠቡ እናቶች መካከል አንዳንዶቹ በሰጡት አስተያየት “አሁን ያገኘሁት ድጋፍ የቆየውን የምግብ እጥረት ችግሩን የሚቀርፍ መሆኑን ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ አሸናፊ ግዛው – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል