በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በ2017 የግብር ወቅት ከደረጃ ‘ሐ’ ግብር ከፋዮች ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱ ተገለጸ
የቢሮ ሀላፊዋ በ2017 የግብር መክፈያ ንቅናቄን አስመልክቶ ለሚዲያዎች መግለጫ ሰጥተዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ አለምነሽ ደመቀ በመግለጫቸው እንዳሉት፤ በክልሉ የተጀመሩ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን ለማሳለጥ ገቢ ወሳኝ መሆኑን አስታወሰው፤ በዘንድሮ የግብር አሰባሰብ ወቅት ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ከሐምሌ 1 ጀምሮ የ’ሐ’ የግብር ከፋዮች ከነገ ሐምሌ ጀምሮ በይፋ ግብራቸውን እንዲከፍሉ ይደረጋል።
በዚህም የ2017 የግብር ዘመን የደረጃ ‘ሐ’ ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብራቸውን በ10 ቀናት ውስጥ ከፍለው እንዲያጠናቅቁ የቢሮ ሀላፊዋ አሳስበዋል።
በንቅናቄው 1 ቢሊዮን ብር ገቢ ከደረጃ ‘ሐ’ ግብር ከፋዮች እንደሚሰበሰብ አውስተው 230 ጊዜያዊ የታክስ መሰብሰቢያ ማዕከላት መዘጋጀታቸውን ወ/ሮ አለምነሽ ተናግረዋል።
በየደረጃው የሚገኙ ተቋማት ለግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ ያሳሰቡት የቢሮ ሀላፊዋ፤ በተለይም 83 ሺህ የ’ሐ’ ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብራቸውን ባሉበት ሆነው በቴሌ ብር መክፈል እንዲችሉ ቅደመ ዝግጅት ሥራ መከናወኑንም አብራርተዋል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ህዝቡ የሚያነሳቸውን የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ ከመመለስ አኳያ የፍትህ ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አሳሰቡ
ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ