በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ
በክልሉ “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ሐሳብ እየተካሄደ በሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብ በቤንች ሸኮ ዞን ሼይ ቤንች ወረዳ ጋይሼማ ቀበሌ ተጀምሯል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ ክልል አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች በይፋ ተጀምሯል።
ሀገራችን ከተረጂነት ተላቃ በምግብ እራሷን እንድትችል የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ወሳኝ ነው ብለዋል።
በዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር 400 ሚሊዮን የሚጠጉ ችግኞች በ3800 ችግኝ ጣቢያዎች መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
በክልሉ ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች በክልላዊ የተከላ መርሐ ግብር በነቂስ በመሳተፍ አሻራቸውን እንዲያሳርፉ ጥሪ አቅርበዋል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብና ቢሮ ሃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው እንደተናገሩት፤ በክልሉ ባለፉት 6 አመታት ከ1.3 ቢሊዮን በላይ ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተተክለዋል፡፡
በተያዘው በክረምት ተከላ ወቅት 196 ሚሊየን 726 ሺህ ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ በቂ ዝግጅት መደረጉን አንስተው፥ ከእነዚህ ውስጥ 60 በመቶ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መሆናቸውን አብራርተዋል።
ባለፉት አመታት የተተከሉ ችግኞች የፅድቀት መጠን 86 ከመቶ መድረሱንም ገልጸዋል።
የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍቲን በበኩላቸው፤ ለግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነት መጨመር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር አይነተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ጦያር ይማም – ከሚዛን ጣቢያችን
More Stories
የህብረተሰቡን ጤና ለማጎልበት የዘርፉን ተግባራት በተገቢው ለማሳካት ከምንጊዜውም በተሻለ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
የህዝቡን የልማት ፍላጎቶች ለማሟላትና መንግስታዊ አገልግሎቶችን በተገቢው ለመስጠት የውስጥ ገቢ ግብርን አማጦ ለመሰብሰብ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተገለጸ
ባለፉት ዓመታት በተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ የልማት ዘርፍ ተጠቃሚነት እየተረጋገጠ መምጣቱን የዳዉሮ ዞን ግብርና፣ የአካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ልማት መምሪያ አስታወቀ