የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች የክልሉን አስፈፃሚ አካላት አመታዊ ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ሁለተኛ ቀን ውሎ እንደቀጠለ ነው
ሀዋሳ: ሰኔ 28/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የክልሉ ምክር ቤት ህግና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ ግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ፣ የፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት የሚከታተሏቸዉን ቢሮዎችና ተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም ግምገማ ዛሬም በማካሄድ ላይ ናቸው።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ፣ የደን አካባቢ ጥበቃና ልማት ቢሮ፣ የሠላምና ጸጥታ ቢሮ፣ የንግድ ገበያ ልማት ቢሮ በዛሬው የጠዋት መርሐ ግብር ሪፖርታቸውን ለአራቱም ቋሚ ኮሚቴዎች በማቅረብ ላይ ናቸው።
ሌሎች ሴክተር መስሪያቤቶችም በወጣላቸው ፕሮግራም መሠረት የሚያቀርቡ ሲሆን፥ የአፈፃፀም ግምገማ መድረኩ እስከ ሰኔ 29/2017 የሚቀጥል ነው።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ