የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች የክልሉን አስፈፃሚ አካላት አመታዊ ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ሁለተኛ ቀን ውሎ እንደቀጠለ ነው
ሀዋሳ: ሰኔ 28/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የክልሉ ምክር ቤት ህግና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ ግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ፣ የፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት የሚከታተሏቸዉን ቢሮዎችና ተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም ግምገማ ዛሬም በማካሄድ ላይ ናቸው።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ፣ የደን አካባቢ ጥበቃና ልማት ቢሮ፣ የሠላምና ጸጥታ ቢሮ፣ የንግድ ገበያ ልማት ቢሮ በዛሬው የጠዋት መርሐ ግብር ሪፖርታቸውን ለአራቱም ቋሚ ኮሚቴዎች በማቅረብ ላይ ናቸው።
ሌሎች ሴክተር መስሪያቤቶችም በወጣላቸው ፕሮግራም መሠረት የሚያቀርቡ ሲሆን፥ የአፈፃፀም ግምገማ መድረኩ እስከ ሰኔ 29/2017 የሚቀጥል ነው።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ