የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች የክልሉን አስፈፃሚ አካላት አመታዊ ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ሁለተኛ ቀን ውሎ እንደቀጠለ ነው
ሀዋሳ: ሰኔ 28/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የክልሉ ምክር ቤት ህግና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ ግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ፣ የፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት የሚከታተሏቸዉን ቢሮዎችና ተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም ግምገማ ዛሬም በማካሄድ ላይ ናቸው።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ፣ የደን አካባቢ ጥበቃና ልማት ቢሮ፣ የሠላምና ጸጥታ ቢሮ፣ የንግድ ገበያ ልማት ቢሮ በዛሬው የጠዋት መርሐ ግብር ሪፖርታቸውን ለአራቱም ቋሚ ኮሚቴዎች በማቅረብ ላይ ናቸው።
ሌሎች ሴክተር መስሪያቤቶችም በወጣላቸው ፕሮግራም መሠረት የሚያቀርቡ ሲሆን፥ የአፈፃፀም ግምገማ መድረኩ እስከ ሰኔ 29/2017 የሚቀጥል ነው።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ