በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚገኙ አገራዊና ክልላዊ የሚዲያ ባለሙያዎች ቡድን በሚዛን አማን ከተማ አረንጓዴ አሻራ ማሳረፍ መርሐ ግብር አከናውነዋል ።
የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ምክትል ቢሮ ኃላፊና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ በረከት እዮብ እንደተናገሩት በክልሉ በነገው ዕለት በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች በይፋ በሚጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር አስቀድሞ የሚዲያ ባለሙያዎች ችግኝ በመትከል በሀገራዊ አረንጓዴ አሻራ መርሃግብር እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል።
የሚዲያ ባለሙያዎች በአረንጓዴ አሻራ ወቅት ኩነቶችን ለህዝብ ከማድረስ ባለፈ ችግኝ በመትከል ሀገራዊ አሻራቸውን ማኖር ይገባቸዋልም ብለዋል።
የደቡብ ራዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ትዕዛዙ ኬንጫ እንደገለፁት የሚዲያ ተቋማት አመራሮችና ባለሙያዎች ዘንድሮ በተለየ መልኩ የችግኝ ተከላ መርሐግብሩ ላይ አሻራቸውን ማሳረፍ በመቻላቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል።
የችግኝ ተከላው ለአከባቢው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን በመግለጽ በየጊዜው ከሚከናወነው ተከላ ባሻገር የተተከሉትን እንክብካቤና ጥበቃ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ግብሩ ላይ የተሳተፉ የሚዲያ ባለሙያዎች በበኩላቸው ዕድሉን አግኝተው አሻራቸውን በማኖራቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።
የሚዲያ ባለሙያዎች እያደረጉ ያሉት የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ተሳታፊዎቹ ገልጸዋል።
በመርሐግብሩ የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ አለሙን ጨምሮ በክልሉ የሚገኙ የሚዲያና ኮሚንኬሽን ተቋማት ባለሙያዎችና እንዲሁ የደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ሚዛን ቅርንጫፍ አመራርና ሰራተኞች ተሳታፊዎች ሆነዋል።
ዘጋቢ፡ ጦያር ይማም ከሚዛን ቅርንጫፍ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል