የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ህግና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ2017 በጀት አመት የአመቱን የሥራ አፈፃፀም እየገመገመ ነው
ሀዋሳ: ሰኔ 27/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ2017 በጀት አመት የአመቱን የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት በዝርዝር መመልከት ጀምሯል።
የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ2017 በጀት አመት የአመቱን ሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡት የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አንዷለም አምባዬ ናቸው።
በቀረበው ሪፖርት ዙሪያ ከቋሚ ኮሚቴ አባላት የተለያዩ ጥያቄና አስተያየት የቢሮ የስራ ኃላፊዎችና የማኔጅመንት አባላት ምላሽና ማብራሪያ ይሰጡበታል ተብሎ ይጠበቃል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ህግና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዱንጋ ናኩዋ ጨምሮ የቋሚ ኮሚቴ አባላትና የተቋማቱ የቢሮ ኃላፊዎች እንዲሁም የማኔጅመንት አባላት እየተሳተፉ ነው።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
ህዝቡ የሚያነሳቸውን የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ ከመመለስ አኳያ የፍትህ ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አሳሰቡ
ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ